ሠላም ጤና ይስጥልኝ ክቡራን አንባቢያን ፤ ከዚህ መካነ-ድር (ድረ ገፅ) ላይ የምትወስዱትን ማንኛውንም ፅሑፍም ይሁን ምስሎች ለአዘጋጆቹ እና ለፀሐፊዎቹ ክብር ሲባል በምትጠቀሙበት ቦታ ሁሉ ምንጩን ትጠቅሱልን ዘንድ በትህትና እናሳስባለን ፡፡

Thursday, March 22, 2012

ውሀ ያስፈልጋቸዋል!!

ይህች ሳምንት በኢ.... ታሪክ ታልቅ ታሪክ የተሰራበት፤ ምን ያህልም እምነታችንን፣ ሀይማኖታችንን፣ ታሪካችንን እንደምንወድ እንደምናከብር እንዲሁም ህይወታችንን አሳልፈን ለመስጠት እንደማንሳሳ የታየበት ወቅት ነው፡፡ መከራ ይምጣ ባይባልም፤ ችግር ይፈትነን ባይባልም በአንድም በሌላ መንገድ ሊያስተምረን፣ ሊያስጠነቅቀን፣ ምን ያህል ለእምነታችን እንደምንቆም መፈተኛም ሊሆን ይችላል፡፡ የነበረውን ህብረታችንን እንውደደው፤ ከበረታንም አንድ የምንሆንበትን ሁኔታ እናመቻች፡፡ እርግጥ ነው አንድ ነን፤ይህም  በዚህ ታሪካዊ ሳምንት መታየት ችሏል፡፡
ይኸው ቀናቶች ገፉ የዝቋላ ደንም እፎይ ማለት ጀምሯል፡፡ ሰላማዊ አየርም ይነፍስ ጀምሯል እናቶቻችን አባቶቻንን መረጋጋት ጀምረዋል፡፡ ይህ ስሜት አዲስ አበባም ባህር ዳርም፤ ናዝሪትም በሁሉም ቦታዎች በትንሹም ቢሆን እየመጣ ነው፡፡ እርግጥ ነው በገዳሙ ስራ ተጀመረ እንጂ ገና አላለቀም፡፡ አሁንም ብዙ ሰዎች አካባቢውን ማየት ወደ ቦታውም መሄድ ይሻሉ፤ ማድረግ ያለባቸውንም ለማድረግ አቆብቁበዋል፡፡ በወቅቱ ወደ ቦታው የተመመው ህዝብም ተልዕኮውን ፈፅሞ ቀጣዩን ስራ ደግሞ ለሚቀጥለው ተተኪ ትቶ መመለስ ጀምሯል፡፡ እንኳን ደህና መጣችሁ እላለሁ ነገር ግን አሁንም አካባቢው ላይ ያሉ ታላላቅ አባቶቻችንና እናቶቻችን ለደረሰባቸው ድንጋጤና መረበሽ አይዟችሁ የሚላቸው ያስፈልጋል፡፡  አሁን እየታየ ያለው ሁሉም እራሱን ለማረጋጋት ሲሞክር ነው፡፡ ይህ መልካም ነው እግዚአብሄር ያበርታችሁ ብያለሁ፡፡ እንደተነገረኝ በዚህ ወቅት ችግር እየሆን ያለው በቂ የሆነ የሚጠጣ ውሀ ማጣት ነው፡፡ ቦታው ላይ ያሉ አባቶች እንዳሉት ሁሉም ነገር እየተረጋጋ ቢሆንም አሁን ወደ ቦታው ለሚሄዱ ሠዎችም እንዲተላለፍ የፈለጉት በተቻለ አቅም የውሀ አቅርቦት ከፍ እንዲልላቸው ነው፡፡ ውሀ ያስፈልጋቸዋል!! ስለሆነም አይደለም ዉሀ ሌላም ቢታዘዝ ወደኋላ የማይለው ምዕመን ይህንን ችግር አይቶ አስቸኳ ምላሽ ይሰጥ ዘንድ በትዕትና እጠይቃለሁ፡፡

በመጨረሻ በመጪው ቅዳሜ እና እሁድ ወደ ዝቋላ በመሄድ እርዳታችሁን ልታደርጉ የተዘጋጃችሁ ካላችሁ በ 0922-123458 ደውሉልኝና መረጃውን ለህዝብ እናሳውቅ ፡፡

No comments:

Post a Comment