tag:blogger.com,1999:blog-37886423893414623242024-02-23T10:43:08.233+03:00የብስራት እይታ Bisrat's Viewእምነቴ -> ማንነቴ ፤ ማንነቴ -> ኢትዮጵያዊነቴ ፤ ኢትዮጵያዊነቴ -> ኩራቴ !Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.comBlogger128125tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-72869186110887134222022-12-22T07:54:00.005+03:002022-12-22T08:22:54.027+03:00ደብረ ዓባይ አቡነ ሳሙኤል ገዳም - ታኅሳስ 12<p> አባታችን አቡነ ሳሙኤል ደብረ ዓባይንና ዋልድባን ያቀኑ ታላቅ ጻድቅ ሲሆኑ የተወለዱት ቦታም በትግራይ ክፍለ ሀገር በርዕሰ ገዳማት ወአድባራት አክሱም ጽዮን በ 1298 ዓ.ም ከአክሱም ባላባቶች እና ካህናት እንዲሁም የአክሱም ጽዮን ገበዝ ከሚሆን ከጌዴዎን ዘር ከእስጢፋኖስና ከዓመተ ማርያም ተወለዱ።</p>
በተወለዱም በ7 ዓመታቸው ወደ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ገብተው በአጭር ጊዜ ትምህርታቸውን አጠናቀው በ 1314 ዓ.ም መንነው ወደ ደብረ በንኮል ገዳም ገብተው በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ መነኮሱ። በደብረ በንኮል 3 ዓመት በርድና 9 ዓመት በምንኩስና ጠቅላላው 12 ዓመት አገለገሉ። ከዚያ በኋላ ከዚያ ወጥተው ወደ በጌምድር በመሄድ በወይና ፣ በመንዳባ ፣ በዞዝ ፣ በአዘዞና በአብጠራ ወዘተ እየተዘዋወሩ በየዋሻው ሱባዔ እየገቡ በጾም በጸሎት በስግደት በአርምሞ በተለያየ ገድል 19 ዓመት ከተቀመጡ በኋላ ወደ ሽሬ አውራጃ ተመልሰው በየቦታው እየተዘዋወሩ የገበሬዎችን ዘር እየባረኩ ሕሙማንን እየፈወሱ ሙታንን እያስነሱ ትምህርተ ወንጌልን እየሰበኩ ብዙ ሕዝብን ካሳመኑ በኋላ በ1353 ዓ.ም ወደ ደብረ ዓባይ ገቡ። ገብተውም የቦታውን ጽሙናና የቦታውን ስፋት አይተው በጣም ተደስተው ሱባዔ ቢገቡ ብዙ ተአምራት ተደርጎላቸዋል። <div><span></span>ከተአምራቶቹም ጥቂቶቹ ውዳሴ ማርያምን እና ቅዳሴ ማርያምን ደግመው ውሃውን ቢባርኩት ኅብስት ሆኖላቸው አርድእቶቻቸውን መግበዋል። <br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;"><a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjLS3I49rmdMZdssdzJ3V_3f5DD21sCC2qB0GOJMmGVjdCNviiStUVbeDP69Su27Rg77FL1hACzClTGH3NFCdbsvwFFT1-qbDH3YqaWVXsA4OTXNz-q8-_h2mbdhInLCHpporL0e4gCisYJ3uM6NUcd3EwdLBxidcGGfx9PiNYGMIRHgWsCJMtO6fgm/s715/PSX_20221222_021137.jpg" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="402" data-original-width="715" height="180" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjLS3I49rmdMZdssdzJ3V_3f5DD21sCC2qB0GOJMmGVjdCNviiStUVbeDP69Su27Rg77FL1hACzClTGH3NFCdbsvwFFT1-qbDH3YqaWVXsA4OTXNz-q8-_h2mbdhInLCHpporL0e4gCisYJ3uM6NUcd3EwdLBxidcGGfx9PiNYGMIRHgWsCJMtO6fgm/s320/PSX_20221222_021137.jpg" width="320" /></a></div><br />እስከ ዛሬ ድረስ ገዳሙ የሚገለገልበት "ማይ ምንጭ" የሚባለውን ውሃ ባርከው አፍልቀዋል። ቅዱስ ሚካኤል ወደ ሰማይ አሳርጎ የሰማይ መኖሪያቸውን አሳይቷቸዋል። እራሱ ጌታችንም ከንጽሕት እናቱና ከአእላፍ መላእክት ጋር ሰማያዊ የመድኃኔዓለም ታቦትን ይዞ መጥቶ ሰጥቷቸው ይህች ቦታ ቦታህና መካነ ርስትህ ናት ብሎ ቃል በቃል ተነጋግሯቸው ዐርጓል።<br />
በተነጋገሩበት ቦታ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተሰርቶበት እስከ ዛሬ ድረስ ይገኛል። <span><a name='more'></a></span>ደብረ ዓባይ ሆነውም ወደ ዋልድባ ሲመለከቱ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ ከምድር እስከ ሰማይ ደርሶ ታያቸው። ምን ይሆን እያሉ እያደነቁ ሲኖሩ ከዕለታት በአንድ ቀን ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ "ያየኸው ዓምደ ብርሃን በቦታው ልጆችህ ይኖራሉ። በዚህ ቦታ አበው ተሠውረውበታል። ገዳሙ ከአሁን በፊት በአረማውያን መሪዎች ሁለት ጊዜ ጠፍቷል ። አሁን ግን አንተ እንድታቀናው እግዚአብሔር ፈቅዶልሃል። ብርሃኑም የአንተ ፣ የስውራኑና የልጆችህ ጸሎት ነው።ስለዚህ ተነሳና ወደዚያ ሂድ " ብሎ አዘዛቸው። <div>እዚያው ሄደው ባስለመዱት ገድል ሲኖሩ ዋልድባን እንደመሶብ አንስተው አስባርከዋታል።በዚሁ ቦታ በግብረ አምላክ ከሰማይ የመሥዋዕት ዕቃዎችና መሥዋዕት ወርዶላቸው የእመቤታችን ቅዳሴ ቀድሰው ሥውራኑንና ያልተሠወሩትን አቁርበዋቸዋል። እስከ ዕለተ ምጽአት የሚወለዱ ልጆቻቸውን አሳይተዋቸዋል።</div><div> <div class="separator" style="clear: both; text-align: center;"><a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg57zNc_8Qkry61SL5pmvEeb8K0MvunqRouTe5tvRyvPLdgKhzhqwPb8dwFL7Xo3EVKXSPIyKoheYu-EDubRoVDsOV1UNsltQrFkZC8KUZdGVvWrcY2ctVNYrEj4SWEnyfXudDlA2-FZurur789FH8ZviBPdKJtUlAzbhXYblyM7HSL0YJEpOHETgyb/s1248/1671663945929.jpg" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="1248" data-original-width="715" height="262" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg57zNc_8Qkry61SL5pmvEeb8K0MvunqRouTe5tvRyvPLdgKhzhqwPb8dwFL7Xo3EVKXSPIyKoheYu-EDubRoVDsOV1UNsltQrFkZC8KUZdGVvWrcY2ctVNYrEj4SWEnyfXudDlA2-FZurur789FH8ZviBPdKJtUlAzbhXYblyM7HSL0YJEpOHETgyb/w150-h262/1671663945929.jpg" width="150" /></a></div><br /></div><div>እንዲህ እያሉ በዋልድባና በደብረ ዓባይ እየተዘዋወሩ ሲኖሩ ወደ ቅርብ በአንበሳ ወደ ሩቅ በክንፈ ብርሃንና በሠረገላ ብርሃን እየሆኑ ይሄዱ ነበር። በሕይወታቸው ሳሉ 700 ያህሉ የመንፈስ ልጆች ነበሯቸውና በዋልድባና በደብረ ዓባይ ማህበር ሠርተው እያስተዳደሩና እያስተማሩ ሲኖሩ በዚሁ ገዳም 45 ዓመት እንደተቀመጡ በ 100 ዕድሜያቸው ታኅሳስ 12 ቀን ማክሰኞ ዕለት በ1398 ዓ.ም በደብረ ዓባይ አረፉ።በተቀበሩበት በደብረ ዓባይ ገዳም በፀጋ የተሠጣቸው የመዝገብ ቅዳሴ ጉባዔ ሲወርድ ሲዋረድ እስከ ዛሬ አለ። በኢትዮጵያ ደረጃ የመዝገብ ቅዳሴ ማስመስከሪያ በዚሁ ገዳም ነው። የከብት ቆዳ በተአምራት እንደ በርሜልና እንደ ጋን ለክብረ በዓላቸው ለጠላ መጥመቂያ ያገለግላል።ያገለገለውን ሲያረጅ እየተቆረጠ ለእምነት ይሰጣል። ከተለያየ አደጋና በሽታም ያድናል። <br />
ስለዚህ እንደ አክሱም ኅዳር ጽዮን ፣ እንደ ግሸን ማርያም እንደ ላሊበላ እንደ ዋልድባ መጋቢት 27 እና ጥር 11 በዚሁ በደብረ ዓባይ ገዳማቸው ብዙ ምእመናን በየዓመቱ ታኅሳስ 12 ቀን እየመጡ በዓሉን አክብረው ይውላሉ። ስለዚህ ከቅርብም ከሩቅም በንጹሕ ልቡና የተማፀነና የተሣለ ሁሉ የለመነውን ያገኛል። ይደረግለታልም።<br />
<br />
አምላከ አቡነ ሳሙኤል ከቦታው ተገኝተን የጻድቁን በረከትና ረድኤት ለመሳተፍ ያብቃን ። <br />
<br />
አሜን።<br />
<!--/data/user/0/com.samsung.android.app.notes/files/clipdata/clipdata_221222_014021_892.sdoc--></div><div class="separator" style="clear: both; text-align: center;"><a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgRnCaZF5tswUqFQfRwSaoN_2NwhSDATBlk5VTSX6r3Sb9PuZeJqbUvWQ2E190OYCM5VkRyfSGIneZAOgZ4MMSzBIQX2tom812XSvtvNN4bT2x45k1nFsKRGPKrkDFZoFn4Gj4jWBisHlYSIzv0vrN7i0BE0uqDj8C3qozgM6ABIOoUnw0fFYoeHVhE/s480/1671664056389.jpg" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="319" data-original-width="480" height="190" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgRnCaZF5tswUqFQfRwSaoN_2NwhSDATBlk5VTSX6r3Sb9PuZeJqbUvWQ2E190OYCM5VkRyfSGIneZAOgZ4MMSzBIQX2tom812XSvtvNN4bT2x45k1nFsKRGPKrkDFZoFn4Gj4jWBisHlYSIzv0vrN7i0BE0uqDj8C3qozgM6ABIOoUnw0fFYoeHVhE/w286-h190/1671664056389.jpg" width="286" /></a></div><br /></div>Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-13229556063100907572022-05-25T13:36:00.000+03:002022-05-25T13:36:06.383+03:00ኦርቶዶክሳዊነት እና የሰይጣን መንግስት <p></p> ላለፉት ዓመታት ማህበራዊ ገጾችን በተለይ ፌስቡክን ለምፈልገው ዓላማና ግብ ስጠቀምበት ነበር። ይሁንና ከጥቂት ዓመታት ጀምሮ ግን "እያስጠላኝ" በመምጣቱ ምክንያት እንደከዚህ ቀደሙ እይታዬን ፣ ፍላጎቴን ፣ ልምዴን ለማካፈል የነበረኝ ተነሳሽነት እየቀነሰ መጥቷል። በዚህም የፌስቡክ ጥቅም ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ምን እንደሆነ እየጠፋኝ እና እየዘነጋሁት መምጣት ጀምሯል።<p></p><p>ይኼ ሁኔታ ልክ ይሁን ልክ አይሁን አሁን ላይ ማሰብ ባልፈልግም እንደዛሬው አይነት ጉዳይ ሲገጥመኝ ግን እንደሁኔታዎች እራሴን መፈተሽ እንዳለብኝ ተሰምቶኛል።</p><p>ከአንድ ወዳጄ ጋ ሻይ ቡና እያልን ስለሀገራችን አኹናዊ ሁኔታ ስንጫወት በመሐል ኦርቶዶክሳዊነት እና ብልጽግና ስለሚባለው ኮተት መዋቅር አንስተን መጫወት ጀመርን። ጥሩ ጥሩ ሃሳቦችን አንሸራሸርን። አድምቀን አድምተን ተወያየን።</p><p>በመሐል </p><p>" ብስሬ የመምህር ፋንታሁን ዋቄን አዲሱን መጽሐፍ ገዝተህ አንብበው ፤ ምን ያህል ኦርቶዶክሳዊነትን ለማጥፋት እየሰሩ እንዳለ ግንዛቤ ይሰጣል " አለኝ።</p><div class="separator" style="clear: both; text-align: center;"><a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhoDyA96WiTkJ-LgigK6u7TdvHe_9huHcga2GNMnNrYz6s52MAPHcPcUAVwq8b4YAVf0hm18z3JPCDE4luQXIHgfWyxFNJxsLaRKQFoVo6dM0t3ufAAaS-QTEe_VbD4pS4GH-zpKecG9Sk2Ds5SBTBCcyzBDfqu5g0VOo6MxAKESQYTiRtGWno-jJ9Q/s1240/284123990_5071017449613524_52637671324410580_n.jpg" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="1240" data-original-width="874" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhoDyA96WiTkJ-LgigK6u7TdvHe_9huHcga2GNMnNrYz6s52MAPHcPcUAVwq8b4YAVf0hm18z3JPCDE4luQXIHgfWyxFNJxsLaRKQFoVo6dM0t3ufAAaS-QTEe_VbD4pS4GH-zpKecG9Sk2Ds5SBTBCcyzBDfqu5g0VOo6MxAKESQYTiRtGWno-jJ9Q/w226-h320/284123990_5071017449613524_52637671324410580_n.jpg" width="226" /></a></div><p></p><p>ለጥሩ ውይይት ትክክለኛ ግብዣ ብዬ መጽሐፉን ማንበቤን ልነግረው አልኩና ስለመጽሐፉ የተሰማውን በዝርዝር እንዲያወራ ስለፈለኩ ተውኩት። </p><p>መጽሐፉ፦<span></span></p><a name='more'></a><p></p><p><span></span>"ኦርቶዶክሳዊነት እና የሰይጣን መንግስት " የተሰኘ ርዕስ አለው። ውርስ ትርጉም ነው። መምህር ፋንታሁን ዋቄ ደግሞ በጥሩ ሁኔታ አዘጋጅቶና ተርጉሞ ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን በኃላፊነት መንፈስ አዘጋጅቶ አቅርቦልናል።<br /><br />ግን ግን ስንቶቻችሁ አንብባችሁታል?</p><span></span><p>ካላነበባችሁት ዳይ አሁኑኑ መጽሐፉን ግዙና አንብቡት።</p><p>ትዕዛዝ ነው!!</p><p>ያው እኔ የምመርጥላችሁን ደግሞ ታውቁም የለ፦ የሚጠቅማችሁን ነው።</p><p>ምነው ብስራት ማስታወቂያ አስመሰለብህ ብትሉኝ ደግሞ መልሴ... አዎ በሶስት ምክንያቶች ማስታወቂያ ሊሆን ይችላል እላለሁ።</p><p>☝️የመጀመሪያው</p><p>ኦርዶክሳዊነቴ እና በእምነቴ ዙሪያ ያንዣበበውን አደጋ ለተቀረው አማኝ ማሳወቅ እና ማስተማር እንዴት ብሎም እምነቱንም ሀገሩንም እራሱንም መጠበቅ እንዳለበት ግንዛቤ እንዲወስድ ስለምፈልግ ነው። </p><p><img border="0" data-original-height="1000" data-original-width="1250" height="256" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhqd_NmqEX7efp27u_rydoOGwF2u63IPeukiBotClhl4RF8EADBbv3Ua2Kqt1kVTF4U1sDb9gj-rVs7-iN91vvQazPRVMTBgdwygOBr1EUHIu-34bkSAdNTqn7qjiVl5jgbxiFnfa8Sdgbso1_F3VbMre_VjxeDPxsp4gp3fPFAK_PColfL8QEHyZ8E/s320/284129533_5071017446280191_2083741120392452921_n.jpg" width="320" /></p><p>☝️ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ የመጽሐፉን የሽፋን ስዕን ዲዛይን በመስራት የተሳተፍኩ መሆኔ የልብ ልብ ሰጥቶኝ ነው። ይሄ ምክንያቴ ለመጽሐፉ ማስታወቂያነት አንተን ወይም አንቺን ለማነሳሳት ብዙም ባይጠቅምም ድንገት ግን እንደተጨማሪ ማነሳሻ መጽሐፉን ለመግዛትና ለማንበብ ፍላጎት ካሳደረባችሁ ብዬ ነው።</p><p>☝️ሶስተኛው ኦርቶዶክስ ሆኖ ሀገሩንም የሚወድ ነገር ግን የተዘናጋም የተኛም ያንቀላፋም ካለ ለመቀስቀስና እራሱንና ቤተክርስቲያኑን ሀገሩን መጠበቅ እንዳለበት እንዲያስብ ለማድረግ ነው።</p><p>እሹሩሩ አልኳችሁ አይደል?</p><p>በሉ አሁኑኑ ፈልጉና ግዙት። ኦርቶዶክሳዊ ከሆናችሁ ለራሳችሁም ለቀጣዩም ትውልዳችሁ ለልጅ ልጆቻችሁ ማሰብ ግዴታችሁ ነው። በተጨማሪም ለወዳጅ ዘመድ አካፍሉት። ለታሪክ አስቀምጡት።</p><p>ወደመነሻዬ ስመጣ ፌስቡክን በመጥላቴ ለህትመት ከበቃ ወራትን ያስቆጠረውን ይህን መጽሐፍ ሳላስተዋውቃችሁ ሳልጋብዛችሁ በመቅረቴ ይቅርታ እየጠየኩኝ መጽሐፉን በተመለከተ በተለያየ መንገድ (Share , Like , comment) ለምታስተዋወቁ አስር (10) ወዳጆቼ መጽሐፉን ገዝቼ እንደምሸልማችሁ መግለጽ እወዳለሁ።</p><div class="separator" style="clear: both; text-align: center;"><a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiQ5R29STwFzWFajW0W0DYXiiyg0ElH38LjSOtWowusQhyZYALEb-DIT4AfAuyp4NLihffoX7v--OGWcaC95SjT7i36zZbWeoZdVo2NHVambm-CuRElXJXknBKlDm2Fg31nlqvvSrivZAyEVCZbiu1r4E5a55ASoh-p_kd3QsXdxIlGAwmcBm9XyWye/s1250/283940485_5071017469613522_496960009276305754_n.jpg" style="clear: left; float: left; margin-bottom: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="1000" data-original-width="1250" height="256" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiQ5R29STwFzWFajW0W0DYXiiyg0ElH38LjSOtWowusQhyZYALEb-DIT4AfAuyp4NLihffoX7v--OGWcaC95SjT7i36zZbWeoZdVo2NHVambm-CuRElXJXknBKlDm2Fg31nlqvvSrivZAyEVCZbiu1r4E5a55ASoh-p_kd3QsXdxIlGAwmcBm9XyWye/s320/283940485_5071017469613522_496960009276305754_n.jpg" width="320" /></a></div><p></p><p><br /></p><p><br /></p>Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-48685361262239859102018-07-11T20:44:00.003+03:002022-05-25T12:46:16.410+03:00ማነው ገንጣዩ?<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<span style="font-size: small;"> <span style="font-size: xx-small;"> <span style="font-size: small;">የዚህ ፅሑፍ መነሻ አንድ የማከብረው ወዳጄ 'ትግራይ' ብትገነጠል ምንም አናጣም... የትግራይ ሠው ማለት እንደዚህ ነው... ትግሬ ማለት እንደዚህ ነው... እያለ የወረደ እና የሚያበሳጭ ፍሬአልባ ፅሑፍ ፅፎ ማየቴ ነው። የገረመኝ 'ተደምሬያለሁ' የሚል ቲሸርት ለብሶ ፈገግ ኮራ ብሎ የተነሳውን ፎቶ ጨምሮበታል።</span></span> እርግጥ ነው በሒሳብ ስሌት 'መደመር' ገደብ የለውም። ከማንም ጋር ከምንም ጋር መደማመር ይቻላል። ውጤቱም እንደተደማሪው ዓይነት ፣ ይዘት ይወሰናል። እንግዲህ ከማን ጋር እንደተደመረ እሱ ይወቀው።</span><br />
<span style="font-size: small;">ሠሞነኛው ሙቀት መሠለኝ አሁን አሁን በተጠናከረ ሁኔታ ስለ ትግሬ እና ትግራይ መልካም ነገር እየተነገረ አይደለም። ምንም እንኳን ጥቂቶች በተቃውሞ ቢሟገቱም!</span><br />
<br />
<span style="font-size: small;"><span style="font-size: xx-small;"> </span><span> "ስታጠፋ ምላስ እንጂ አቋም አያስፈልግም" እንደሚባለው አንዳንዶች ጥላቻን ለማስፋፋት ፈለገው ፣ አንዳንዶች በአለማወቅ ፣ በአስተሳሰብ ጥበት ፣ ሌሎች 'ትገንጠል አታስፈልግም' በማለታቸው የሚበላ ትርፍራፊ እንጀራ በማግኘት ይኖራሉ። ሁሉም ግን አይረቡም። </span></span><br />
<span style="font-size: small;">እንደዚህ የወረደ ፣ ታጥቦ የማይጸዳ ፣ የመነቸከ ስብዕና ተሸክመው የሚኖሩ እነሱንም በመደገፍም በማራገብም ከጎናቸው የሆኑ ሁሉ 'ትግራይ' ሳትሆን እራሳችሁ ከህዝቡ ከማህበረሰቡ ብትገነጠሉ ለኢትዮጵያ ትልቅ አስተዋጽዖ እና ዘላቂ ጥቅም ነው። ችግሩ ተገንጠሉም ብትባሉም ይህን የሚያስደርግ ወኔም ድፍረትም የሌላችሁ መሆኑ ነው። እንደመርዘኛ እባብ ተሸሽጎ የጥላቻ የመከፋፈል ቃላትን መወርወር ካልሆነ።</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span><span style="font-size: small;">
<span style="font-size: xx-small;"> <span style="font-size: small;">ባለፉት 27 ዓመታት መገነጣጠል መከፋፈል ብዙ ዋጋ አስከፍሎናል። ያለንን ደም መጦ ጨርሶ በአጥንታችን አስቀርቶ ተፈታትኖናል ፤ ጥንካሬያችንን ሰብሮ ህብረታችንን በትኖ ፍቅራችንን አጠልሽቶ ክብር አልባ ሀገር አልባ ወገን አልባ ዕምነት አልባ ሊያደርገን ሞክሯል።</span></span></span><br />
<a name='more'></a><span style="font-size: small;">ስለመገንጠል ስለመጠላላት ስለዘረኝነት የሚያስብ ላይ ይቅር መባባል መደራደር ተገቢ ነው ብዬ አላምንም። ማንም እየተነሳ ስለሌላው ህዝብ እንዲያወራ መፈቀድም አለበት ብዬ አላምንም። ቀልድ ጨዋታ መፎጋገር የትም ዓለም አለ። አንዱ በአንዱ መተራረብ በአኗኗር መንገድ ውስጥ የሚታይን እውነታ ማሳያ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አንዱ በአንዱ ጥላቻን ቂምን መዝራት ግን አንገት ማስቆረጥ አለበት ብዬ አምናለሁ።</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span><span style="font-size: small;">
<span style="font-size: xx-small;"> <span style="font-size: small;">እኔ የትግራይ ተወላጅ አይደለሁም ነገር ግን ስለ ትግራይ ሕዝብ መልካምነት እስከጥግ ልናገር ፣ እስከጥግ ልሟገት እችላለሁ። ኢትዮጵያን እንደቅርጫ አከፋፍለህ ለኢትዮጵያ የሚጠቅሟትን የሚያስፈልጓትን ክልሎች አስቀር ብባል ከማስቀራቸው ክልሎች አንዷ ነች። ይህ ማለት ሌሎቹ አያስፈልጉም ሳይሆን በባህል በታሪክ በዕምነት በሌሎችም ብዙ ምክንያቶች ትልቅ ቦታ ስላላት ነው።</span></span></span><br />
<span style="font-size: small;">ስለሌሎቹ ታውቃለህ ወይ ብትሉኝ መልሱ አዎ ነው። ኢትዮጵያን ከእግር እስከ እራሷ አውቃታለሁ ነው መልሴ!!! በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ዞሬያለሁ ፣ ከርሜያለሁ ፣ ኖሬያለሁ ሰንብቻለሁ። ባለጌውንም ሌባውንም ግብዙንም ቅኑንም ደጉንም ታሪክ ሳይኖረው እዚህ ግባ የማይባል ወሬ ይዞም ታሪኬን አክብሩልኝ ብሎ ዘራፍ የሚለውንም ለይቼ አውቃለሁ።</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span>
<span style="font-size: small;">የፍቅር ከተማ ነን ፣ የባህል ማዕከል ነን ፣ ትንሿ ኢትዮጵያ ነን ፣ የሃይማኖት መቻቻል ማሳያ ነን... ሌላም ሌላም እያሉ እራሳቸውን በራሳቸው ሾመው እራሳቸውን እያወደሱ ስራቸው ምግባራቸው ግን የላሸቀ ምንም ከሚሉት ጋር የማይገናኙ ክልሎችን ቦታዎችን ህዝቦችን አውቃለሁ።</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span>
<span style="font-size: small;">በኢትዮጵያዊነታችን ተመሣሣይነታችን ብዙ እንደሆነ ሁሉ ምንም ኢትዮጵያዊነት ምንም የማይታይባቸው ሆዳም ለሆዳቸው የሚያድሩ ሠውን የማያከብሩ ፣ እንግዳ ሲመጣ አሳቀውና አስጨንቀው ምን ዓይነት ህዝቦች ናቸው እነዚህ የሚያስብሉ ሠውን የማያከብሩ ፣ እንግዳ ሲመጣ አሳቀውና አስጨንቀው ምን ዓይነት ህዝቦች ናቸው እነዚህ የሚያስብሉ ሠውን እንደከበት እያረዱ የሚደሠቱ፣ሠው ሲሞት የሚስቁ ፣ አውሬ ከአውሬ የባሱትንም ዘርዝሬ ልናገር እችላለሁ። እድፍ ጉድፋችንን ሸፍነን ስለሌሎች ለምን እንደምናወራ አይገባኝም።</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span>
<span style="font-size: small;">በተለይ በዚህ ወቅት ዝቅ ብሎ እግር የማያጥብ ሁሉ ስለኢትዮጵያዊነት ህብረት ለማውራት ሲዳዳው ስመለከት አፍራለሁ። እነእንትና አይጠቅሙም ፣ እነእንትና ልሙጡን ባንዲራ ለምን ያዙ? እነእንትና እኮ እንዲህ ናቸው... ብላብላ መጀመሪያ እራሳችንን እንፈትሽ!! ለኢትዮጵያዊነት የሚያበቃ ኢትዮጵያዊ የሚያደርግ ማንነት ስብዕና የተወለወለ ታሪክ አለን ወይይ እንበል። እኛ ለማንታመንለት ኢትዮጵያዊነት ሌሎችን ማጥላላት ዋጋ የለውም።</span><br />
<span style="font-size: small;">"ግም ለግም አብረ አዝግም" ለሀገር አይሰራም።</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span><span style="font-size: small;">
<span style="font-size: xx-small;"> የኢትዮጵያን ታሪክ እና መገለጫዎች የያዘውን እና ተጨፍልቆ የሚኖረውን የሌሎች መጠቀሚያ ከሆነው የትግራይ ነዋሪ ይልቅ ከአስቸጋሪነታቸው የተነሳ መግባባትን የማይመርጡ ብናጠፋም ቻሉን መቻቻል ግድ ነው ብለው የሚሰብኩ ሰብዓዊነት የሚባል ነገር ያልፈጠረባቸው ሠው ሠው የማይሸቱ የወረዱ ህዝቦች ነዋሪዎች ተወላጆች ቢገነጠሉ ምርጫዬ ነው። ይሄንን ሃሳቤን ሀገርን የሚዞሩ ሠዎች ያውቁታል ይረዱኛልም ብዬ አስባለሁ። እውነታን እየሸፈኑ ታሪክን እየደበቁ እስከመቼ እንደምንዘልቅ አልገባህ ብሎኛል።</span></span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span>
<span style="font-size: small;">ከተማ እየኖረ የበሰለ እየበላ ንጹህ ውሃ እየጠጣ ያማረውን እየለበሰ ነገር ግን ስለማያውቀው ህዝብ ፣ የህዝብ አኗኗር ፣ ስለማያውቀው ባህል ፣ ስለማያውቀው ታሪክ ፣ ስለማያውቀው ነገር... የሚያወራ ሠው እንዴት እንደሚሰማ እንዴት እንደሚደመጥ እንዴት ዝም እንደሚባል ግራ ይገባኛል። የአጨብጫቢውስ መብዛት? ያስደንቀኛል።</span><br />
<span style="font-size: small;">"ደሃ ተበድሎ ይቅር በሉኝ ይላል" አለ የሀገሬ ሠው።</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span>
<span style="font-size: small;">እዚህ ላይ ለሆዳቸው ያደሩ አዲስ አበባ ላይ እና ከኢትዮጵያ ውጪ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ የስርዓቱ ደጋፊዎች እና ፍርፍር ጠባቂ ለቃሚዎች ይኖራሉ። ቆሻሻ ሕይወት እየኖሩ በችግሮቻችን የሚስቁ አሽቃባጭ አቃጣሪዎች ሞልተዋል። ሲያበሳጩን ሲያስገድሉን ሲያስመቱን ሲያሳስሩን የኖሩ አሉ። ከእነሱም ጋር ተደምረው ህዝብን ሲያስለቅሱ የነበሩ ያሉ የሌላ ብሔር ተወላጆችም እንዳሉ ማለት ነው! ታዲያ ይሄን ለይተን ውቧን ኢትዮጵያ መፍጠር እንዴት ያቅተናል? ዘለዓለም መበላላት?</span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span><span style="font-size: small;">
<span style="font-size: xx-small;"> የሚጻፉልን የተጣመሙ መጻሕፍት የሚነገሩን የውሸት ታሪኮች የምንመለከታቸው የፈጠራ ፊልሞች ገንዘብ አፍቃሪነታችን አጣመውን ሊሆን ይችላል። ቢሆንም ስለኢትዮጵያዊነት ስናወራ ምክንያታዊነት እንጂ ተደማጭነት ስላለን ፣ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ ምዑር ስለሆን ፣ ታዋቂ ስለሆን ፣ መጻፍ ስለምንችን ፣ ወሬኛነት ስለሚያጠቃን መሆን የለበትም። ምንም ይጻፍ! አይነበብ አልልም ግን በኃላፊነት ስሜት በሚመለከተው አካል ማረጋገጥ ፣ ተገቢ ቦታ ሄዶ ማጥናት ፣ አባቶችን አዋቂዎችን መጠየቅ ፣ ሀገሬን ልወቅ ብሎ መነሳት ታሪካዊ ስህተት እንዳንሰራ ይረዳናል።</span></span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span><span style="font-size: small;">
<span style="font-size: xx-small;"> የኢትዮጵያ ፤ የሀገሬ ታሪክ እንደተረት ተረት 'ከዕለታት አንድ ቀን'... ተብሮ ተጀምሮ 'አፌን በዳቦ አብሱ' ተብሎ የሚያቆም አፍ መፍቻ የመላምት መለማመጃ የፈጠራ ውጤት አይደለም። ስለኢትዮጵያ ለማወቅ ፣ ስለቆመችበት ምሰሶ ለመመስከር አርቆ ማሰብ ጠልቆ መመርመር ያስፈልጋል። ለሕጻን ልጅ የማይመጥን የማያሳምን አንደበት ይዘን ስለሀገር መዋቅር ፣ ስለህዝብ ቅንነት ስለግለሰቦች ስብዕና አኗኗር ለመተንተን መድፈር ንቀት ካልሆነ አዋቂነት አይመስለኝም። እንደመር ከሆነ አርፈን እንደመር!!</span></span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span><span style="font-size: small;">
<span style="font-size: xx-small;"> ጊዜው የእርቅ የፍቅር የመተባበር ነው በሚባልበት ወቅት ይህን የሚገልጸውን ባንዲራ አንግበን እየታየን ስለመከፋፈል ስለጥላቻ ስለፀብ የምናወራ ከሆነ ባንዲራውን ሀገራቸውን ለሚወዱ አስረክበን ስለፍቅር ምንነት ፣ ስለባህል ምንነት ፣ ስለአብሮነት ፣ ስለታሪክ ፣ ስለእምነት... በአጭሩ "ስለኢትዮጵያዊነት" ቁጭ ብሎ መማር ሳያስፈልግ አይቀርም።</span></span><br />
<span style="font-size: small;"><br /></span>
<span style="font-size: small;">አመሠግናለሁ!</span><br />
<span style="font-size: small;">ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!</span></div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-34730009965109713772018-04-14T14:04:00.000+03:002018-04-14T14:30:05.555+03:00የዋልድባዎቹ መነኮሳት <div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
በሽብርተኝነት ተከሰው ከሁለት ዓመት በላይ ታስረውን እጅግ የበዛ መከራና ስቃይ ሲቀበሉ የነበሩት ሁለት አበው መነኮሳት ማለትም አባ ገብረኢየሱስ ኪዳነማርያም እና አባ ገብረስላሴ ወልደሃይማኖት ዛሬ ከእስር ተፈተዋል፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ በፊት የአባቶቻችንን መፈታት ደጋግሞ ሲጠይቅ ለነበረው የኢትየጵያ ህዝብ የአባቶቹ መፈታት እንደመልካም ዜና እንደሚያስበው አምናለሁ፡፡ ምክያቱም በወቅቱ አባቶች ይፈቱ በሚለው ድምፅ ውስጥ ሙስሊም ማህበረሰቡም ተሳታፊ የሆነባቸው ወቅቶች ስለነበሩ፡፡<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhuy7t9OjtgsanFlXkfVl2N3jiudAziijWl1F6ODGE7R_dBLqWeNCnSgx9bl9VC-cjHg8PK3XUAP8EHtJFSuXQqZn4n6iRAhpz94K9EAUv2fmKlm8HYcekLljGiA9Yxg_Tdc4VXvJAqog4/s1600/FB_IMG_15236825338787034.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="303" data-original-width="540" height="179" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhuy7t9OjtgsanFlXkfVl2N3jiudAziijWl1F6ODGE7R_dBLqWeNCnSgx9bl9VC-cjHg8PK3XUAP8EHtJFSuXQqZn4n6iRAhpz94K9EAUv2fmKlm8HYcekLljGiA9Yxg_Tdc4VXvJAqog4/s320/FB_IMG_15236825338787034.jpg" width="320" /></a></div>
<br />
ከፍተኛው ፍርድ ቤት በቀን 03 -08 -2010 ዓ.ም የአንድ መቶ አስራ አራት (114) እስረኞችን ክስ አቋርጠናል ብለው ሲገልጹ የአባቶቻችንን ስም ተካቶ የነበረ ሲሆን በዛሬውም ዕለት በቀን አርብ 05 -08 -2010 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ ፍርድ ቤቱ የእስረኛ መፍቻ ደብዳቤ ለቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በመፃፉ ያለወንጀላቸው ሁለት ዓመት በላይ የታሰሩት እስር አባቶቻችን ሊፈቱ ችለዋል፡፡ ለዚህም የብስራት እይታ ድረገፅ አዘጋጆች የተሠማንን ደስታ መግለፅ እፈልጋለሁ፡፡ ይችን ቀን በመናፈቅም ስንጠብቃት ነበር፡፡<br />
<br />
አባቶቻችን ወደበዓታቸው ተመልሰው ለእናት ሀገራችን እንደሚፀልዩ እንደሚያለቅሱ እናምናለን፡፡ ለዚህም የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሆን ዘንድ ምኞታችን ነው፡፡<br />
<br />
ፅሑፌን ከማብቃቴ በፊት አባቶቻችን ከእስር ከተፈቱ በኋላ ለVOA ሬዲዮ የተናገሩትን ታሪክ ተሻጋሪ ንግግር ወደፅሑፍ ቀይሬ እንድታነቡት እጋብዛለሁ፡፡ መልካም የፋሲካ በዓል እንዲሁም መልካም የዳግማ ትንሳይ በዓል ይሁንላችሁ፡፡<br />
<a name='more'></a><br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEifcrMcNMRZllai57gnL2cBk_FKFDbyQObQTetCj9It4dsXqYlsmpjuDcGWpL0t6BJgpOY8fdDWb5hMQT69U6cLTQ4y0XQxEHv0TaUfR930M4eb8ITwwidVBaJJmp-EsMpSnjNXzYNepk8/s1600/FB_IMG_15236829303348250.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="540" data-original-width="540" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEifcrMcNMRZllai57gnL2cBk_FKFDbyQObQTetCj9It4dsXqYlsmpjuDcGWpL0t6BJgpOY8fdDWb5hMQT69U6cLTQ4y0XQxEHv0TaUfR930M4eb8ITwwidVBaJJmp-EsMpSnjNXzYNepk8/s320/FB_IMG_15236829303348250.jpg" width="320" /></a></div>
<br />
አባ ገብረኢየሱስ ኪዳነማርያም<br />
ስለእስር ወቅታቸው ፣ ስለ ገጠማቸው ችግር እና ፈተና አሁን ስለሚሠማቸው ስሜት እንዲሁም ተጠይቀው ሲመልሱ ፦<br />
<br />
" እኛ የታሰርነው ታኅሳስ 28, 2009 ዓ.ም ነው፡፡ ግን ያው የፍርድ ቤት ፣ የማዕከላዊ ፣ የቂሊንጦ ችግር በእኔ አንደበት ብቻ ተገልፆ የሚዘልቅ አይደለም፡፡ ወደፊት ብዙ የምንነጋገርበት ይሆናል፡፡ ለአሁኑ ግን እግዚአብሔር የተመሠገነ ይሁን!በእውነት የአባቶቻችንን አምላክ ከብዙ ፈተናዎች አውጥቶ ከእናንተ ጋር እንድንነጋገር አድርጎናል፡፡ በእውነት እኔ እግዚአብሔርን የማመሠግነው. . . እኛ ደካሞች ብንሆንም ፤ በሕዝባችን ጥረት ፣ በሕዝባችን ትግል ፣ በአባቶቻችንም አምላክ ፤ በአበው አምላክ ፣ ቸርነትና ኃይል የመጣብንን ፈተናና ችግር አስወግዶ አሁን ከወገናችን ፣ ከሕዝባችን ጋር እንድንቀላቀል አድርጓል፡፡"<br />
<br />
ጥያቄ፦ "<br />
በጣም ፈታኝ ችግር ነበር እና ዛሬ ተገላገልን የምትሉት የችግር. . . በነበረው ጊዜ (በእስር ወቅት) ከባድ ጊዜ የትኛው ነበር? "<br />
<br />
" አሁን ተገላግለናል ማለት አይደለም! ችግሩ ይፈታል የምንለው ሀገራችን ፣ ቤተክርስቲያናችን ከታሰሩበት ማነቆ ፣ ከተተበተበው ማነቆ ፣ ሲበጠስ እና ሲፈቱ ነው ከእስር ተፈታን ብለን የምንናገረው፡፡ አሁን ግን ታግተን ነበር ፤ ከእግት ተለቀን ወደ ማህበረሰቡ ፣ ብዙሃኑ ወደ ታሠረበት እስር ቤት ተገናኘን . . . አብረን በአንድ ላይ ተቀላቀልን ማለት እንጂ ከእስር ተፈታን ማለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም በብዙ ነገር ታስረን ነው እየተንቀሳቀስን ያለነው፡፡<br />
<br />
እኛ ውስጥ (እስር ቤት) አካላችን ነው የታሠረው ፡፡ መንፈሳችን አልታሰረም ነበር ፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ቢሆንም ብዙ ወገኖቻችን ታስረዋል፡፡ አሁንም ! አሁንም ከአምስት ዓመት በላይ ፣ አምስት ዓመት ከሶስት ወር ድረስ ያስቆጠሩ ወንድሞቻችን እንደታሠሩ ነው፡፡<br />
<br />
እነ አሸናፊ አካሉ ያለ ከአምስት ዓመት ከሶስት ወር ያለምንም ፍርድ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኝ ወጣት ነው፡፡ እነዚህ እስካልተፈቱ ድረስ ከእስር ተፈታን ብለን ደፍረን ልንናገር አንችልም፡፡ እኛ እነሱ እስካልተፈቱ ድረስ እኛ ተፈታን ልንል አንችልም፡፡<br />
እኛ የምንፈታው አሁንም በእስር ውስጥ ፣ በእገታ ውስጥ ያሉ ወንድሞቻችን ሲፈቱ እና በሀገሪቱ ሠላምና አንድነት ሲረጋገጥ ፤ የመናገር መብት ፣ የመፃፍ መብት ፣ በሀገሪቱ መልካም አስተዳደር ሲሰፍን . . . ያኔ ነው ከእስር ተፈታን ብለን የምንናገረው ፡፡<br />
<br />
ሁለተኛ የእኛን መታሠር ፣ የእኛን መደብደብ ፣ የእኛን መንገላታት ፤ በማዕከላዊም ሆነ በቂሊንጦ የደረሠብንን ግፍ በመስማትና በሬዲዮና በተለያዩ ማህበራዊ ድረገፆች ፣ ሚዲያዎች ሲተላለፍ በመስማት ፤ ተሰባስበው ከቦታው ድረስ መጥተው በመጠየቅ ሙስሊም እና ክርስቲያኑ ሌላም የሌላ ሃይማኖቶች በአጠቃላይ ስለእኛ የተጨነቁ ፣ ያሰቡ ወንድሞቻችን ፣ እህቶቻችን ፣ ወገኖቻችን በሙሉ ፤ ኢትዮጵያዊያን በዓለም ሁሉ የሚገኙ ፣ ሕዝባችንን እጅግ ከፍተኛ አድርገን እናመሠግናለን!! በገዳሙ ስም በዋልድባ ገዳም ስም እጅግ አድርገን እናመሠግናችኋለን፡፡ ምክንያቱም እኛ ከእስር የወጣነው በሕዝባችን ጥረትና ፣ በሕዝባችን አይዟችሁ ባይነት ፣ ሞራል ሰጪነት ፣ ድጋፍ ሰጪነት . . . እኛ ዛሬ ከታገድንበት ቦታ ወጥተን ወገናችንን እንድንቀላቀል አድርገውናል ፡፡ "<br />
<br />
የአባቶቻችንን በረከት ይደርብን!!!<br />
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-73449777505829190752018-01-05T23:47:00.004+03:002018-01-05T23:50:58.404+03:00ኢብራሂም ሻፊ ፦ ነፍስህን በገነት ያኑራት!<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
ኢብሮ የአንተን ማረፍ ስሰማ እንዴት እንዳዘንኩ እንዴት ላሳይህ? ለአንተ ያለኝ ክብር ደግሜ ደጋግሜ ብነግርህም አሁን ሳጣህ ደግሞ የምሆነው ጠፋኝ!<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgDkshmIXI0aGc0M0_99ARNRKN9j-shAceqCSh1ErIGcbuBO9pZtZS7NpyaXQoNF0RwbRkirfYzYg9zGd4eLEPuWOI5-Fc7bEWMOZYsdJ-195p8c7xSxjwYXkOXLSDYEOOLqMkVbnlOWlI/s1600/21541_1330246706892_3372222_n.jpg" imageanchor="1" style="clear: left; float: left; margin-bottom: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="720" data-original-width="570" height="200" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgDkshmIXI0aGc0M0_99ARNRKN9j-shAceqCSh1ErIGcbuBO9pZtZS7NpyaXQoNF0RwbRkirfYzYg9zGd4eLEPuWOI5-Fc7bEWMOZYsdJ-195p8c7xSxjwYXkOXLSDYEOOLqMkVbnlOWlI/s200/21541_1330246706892_3372222_n.jpg" width="158" /></a></div>
በመምህርነትህ ፣ በመጽሔት አምደኛነትህ ፣ በስፖርት ጋዜጤኝነትህ በሬዲዮ በጋዜጦች ፣ በማህበራዊ ገፆች ላይ የምታቀርባቸውን ጥልቅ እይታ ያላቸው ስፖርታዊ ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ ፅሑፎችህ አስተያየቶችህ ንግግሮችህ ስንቱን እንዳስተማርክ ስንቱን እንደለወጠ በምን ቃል ልግለፀው? ለምታምንበት ነገር ሟች እንደሆንክ ከሁሉ በላይ ለእናት ሀገርህ ያለህን ፍቅር ጠንቅቄ አውቃለሁ፡፡ ብዙዎች አቋማቸው እየለዋወጡ ለሆዳቸው በሚኖሩባት ሀገራችን እንዳንተ ያለ በአቋሙ ፀንቶ እራሱንም ለአደጋ አጋልጦ የሚኖር ማግኘት ይከብዳል፡፡ መሰደድህን የሰማሁ ቀን አልቅሻለሁ፡፡ ሀገሬ እንደ አንተ ያሉ ወርቃማ ልጆቿን እስከመቼ እያጣች እንደምትኖር አላውቅም፡፡ አንተ የሆንከውን ስመለከት መጨረሻችን ሁሌም ያሳስበኝ ነበር፡፡<br />
. . . .<br />
<a name='more'></a>እኔና ኢብራሂም ይበልጥ የተግባባነው ከሀገር ከተሰደደ በኃላ ነው፡፡ በሚገርም ሁኔታ ከሀገራዊ ስራዎቼ በተጨማሪ በሃይማኖታዊ ስራዎቼ ላይ እንኳን ሳይቀር አስተያየት ይሰጠኝ ነበር፡፡ ለስራዎቼ ያለውን አድናቆት እና ክብር ብዙ ጊዜ ይነግረኝ ነበር፡፡ ብዙዎች ዕውቀት ሳያንሳቸው በስሜታዊነት እና በጨለምተኝነት በሚኖሩበት በዚህ ጊዜ(ዘመን) ማንም የእሱን ያህል ንፁህ አስተያየት የሰጠኝ ፤ ሃይማኖትህ ሃይማኖቴ ፣ እምነትህ እምነቴ ነው ! አንድ ነን !! ያለኝ የለም፡፡ በዓላት ሲመጡ የእንኳን አደረሰህ መልዕክቶቹ ፤ ሰው አክባሪነቱ ፣ ለሀገሩ ለወገኖቹ ያለውን ተሟጋችነት መቼም አልዘነጋም! ለኔ ዋጋቸው ትልቅ ነበር፡፡ ኢብሮ የዚህ የእብሪተኛው እና የአምባገነናዊ ስርዓት ተጠቂ በመሆንህ ደግሞ ይበልጥ ልቤ ይደማል! እንደ ሰው በሁለት እግርህ በመቆሚያህ ጊዜ በወጣትነትህ. . .<br />
ምን ልበል ወዳጄ የምለው ጠፋኝ እኮ!<br />
ፈጣሪ ነፍስህን ይማር<br />
ሁሌም በልቤ ትኖራለህ!<br />
. . . . .<br />
ለቤተሰቦቹ ለጓደኞቹ ለወዳጆቹ ለጨርቆስ ሰፈር ልጆች ፈጣሪ መፅናናትን ይሰጣችሁ ዘንድ እመኛለሁ፡፡</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-77130064538803799122017-12-12T22:17:00.002+03:002018-01-05T23:52:33.155+03:00በዓታ ለማርያም ( በኣታ ማርያም )<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjKQgzXbjgA0uUJKjd3D-LnbB2I4s-z0p_j8Kwu07Wvham7zGErgVC8PWAiiR9kO6pKwplQUCwpRLQmlm7e33qB0TAyBpxf0npsFWwk2npDAoaEwziA75k1mitYPHmsOKcRzxTLb5mbXnw/s1600/%25E1%2589%25B3%25E1%258B%2595%25E1%258A%25AB+%25E1%258A%2590%25E1%258C%2588%25E1%2588%25B5%25E1%2589%25B5+%25E1%2589%25A3%25E1%258B%2595%25E1%2589%25B3+%25E1%2588%2588%25E1%2588%259B%25E1%2588%25AD%25E1%258B%25AB%25E1%2588%259D.jpg" imageanchor="1" style="clear: left; float: left; margin-bottom: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="623" data-original-width="374" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjKQgzXbjgA0uUJKjd3D-LnbB2I4s-z0p_j8Kwu07Wvham7zGErgVC8PWAiiR9kO6pKwplQUCwpRLQmlm7e33qB0TAyBpxf0npsFWwk2npDAoaEwziA75k1mitYPHmsOKcRzxTLb5mbXnw/s320/%25E1%2589%25B3%25E1%258B%2595%25E1%258A%25AB+%25E1%258A%2590%25E1%258C%2588%25E1%2588%25B5%25E1%2589%25B5+%25E1%2589%25A3%25E1%258B%2595%25E1%2589%25B3+%25E1%2588%2588%25E1%2588%259B%25E1%2588%25AD%25E1%258B%25AB%25E1%2588%259D.jpg" width="192" /></a></div>
በተዋህዶ እምነታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም በምናምነው ዕምነት ሌሎች ከሚቀበሉትና ከሚያምኑት ልዩ ከሚያደርጉት ዓበይት ነጥቦች፦<br />
* በጥፋት መርገም ከአዳም የወረደ የዘር ኃጥያት ያልተላለፈባት ቅድስተ ቅዱሳን<br />
* አስራ ሁለት ዓመት በቤተመቅደስ ማደጓ<br />
* በንፅሕና የተዘጋጀች ፣ በቅድስና ያጌጠች ፣ ቅድመ ፀኒስ ፡ ጊዜ ፀኒስ : ቅድመ ወሊድ : ድኅረ ወሊድ በፍፁም ድንግልና የፀናች ማህተመ ድንግልናዋ የማይናወጥ ዘላለማዊት ድንግል መሆኗን ማመንና ማስተማር ነው።<br />
<br />
የዓለማት ፈጣሪ ልዑል እግዚአብሔር «በልዕልና ሆኖ ተመለከተ: ሁሉ እንደፈረሰ ጆሮ : እንደ ጦር ጎረሮ ተሰተካክሎ በደለ : በጎ ነገርን የሚሰራት የለም» (መዝ, 52) ተብሎ በተነገረለት ትውልድ በአዳም ዘር መካከል በእሾህ ውስጥ እንደ አጌጠች ፅጌሬዳ : በመዓዛ ቅድስና የተጠበቀች ንፅሕ ነፍስ: ንፅሕ ስጋን: ንፅሕ ልቡናን ይዛ የተገኘች የንጉስ ክርስቶስ መቅደስ ድንግል ማርያም ከሁሉ ትበልጣለች… ከሁሉ ትከብራለች። « መልዕልተ ፍጡራን መትሕተ ፈጣሪ » ናት። ከፈጠራት ጀምሮ ስጋዊ ሀሳብ በህሊናዋ ያልተመላለሰ… ከሐልዩ ከነቢብ… ከገቢር የነፃች እናትነትን ከድንግልና አስተባብራ የተገኘች የደናግል መመኪያ ናት።<br />
<br />
<a name='more'></a><br />
« ልጄ ሆይ ስሚ… ምክሬን አድምጪ ንጉስ (ክርስቶስ) ማደሪያው ልትሆኚ ደም ግባትሽን (ቅድስናሽን) ወዶአልና ዘመድሽን እርሺ» (መዝ, 44: 10) ተብሎ በነቢይ እንደተነገረ ለእናትና አባቷ የብፅዕት ልጅ የሆነችው ድንግል ማርያም ሆዷ ዘመድ ሳይወድ… አፏ እህል ሳይለምድ ከእናቷ እቅፍ ተወስዳ ስላሴን እንደአባት … እንደ እናት መላዕክትንእንደእህት እንደወንድም አድርጋ በቤተመቅደስ ያደገች «እህተ መላዕክት» ናት።<br />
<br />
ልጆችን ለቤተ እግዚአብሔር መስጠት… በቤተመቅደስ እግዚአብሔርን እያገለገሉ እንዲያድጉ ማድረግ የልጅ በረከት ለማግኘት የሚናፍቁና እግዚአብሔርን ደጅ የሚጠኑ አማንያን እምነትና ልማድ ነው። እነ ሳሙኤልን የመሳሰሉ ነቢያት ሁሉ በቤተመቅደስ ያደጉ ናቸው።<br />
እመቤታችን ድንግል ማርያም ከሶስተኛ ዕድሜዋ ጀምሮ ከግብር አምላካዊ ከሰማይ የተገኘ ሕብስትን እየተመገበች… ከሰማይ መጠጥን እየጠጣች…ሐርና ወርቅ እያስማማች እየፈተለች በመላዕክት ሞግዚትነት በቤተ መቅደስ ያደገች… በንፅህና በቅድስና የተሸለመች የሰማይና የምድር ማደሪያ (ታቦት) ናት። ንፅሕተ ንፁሐን ድንግል ማርያም እንደዓለም ሴቶች ልጆች በሳቅና ስላቅ … በቧልትና ጨዋታ ያደገች አይደለችም።<br />
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhrHNdam9AiAeZXCjOV-sf8LhrXOHwiHgDj6Jzk8l5yivxabFKDAqpaacze6tp6ANM387TdRPF20s3sSY6az2jnokjBIwJnoms1m3utpOuKGlzAEiMM_QdYkaV-qIAbDFHQKAGwXtRLQAs/s1600/%25E1%2589%2585%25E1%258B%25B1%25E1%2588%25B5+%25E1%258D%258B%25E1%258A%2591%25E1%258A%25A4%25E1%2588%258D+%25E1%2588%2598%25E1%2588%258B%25E1%258B%2595%25E1%258A%25AD%25E1%2589%25B5+%25E1%258B%25B5%25E1%258A%2595%25E1%258C%258D%25E1%2588%258D+%25E1%2588%259B%25E1%2588%25AD%25E1%258B%25AB%25E1%2588%259D.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="327" data-original-width="469" height="223" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhrHNdam9AiAeZXCjOV-sf8LhrXOHwiHgDj6Jzk8l5yivxabFKDAqpaacze6tp6ANM387TdRPF20s3sSY6az2jnokjBIwJnoms1m3utpOuKGlzAEiMM_QdYkaV-qIAbDFHQKAGwXtRLQAs/s320/%25E1%2589%2585%25E1%258B%25B1%25E1%2588%25B5+%25E1%258D%258B%25E1%258A%2591%25E1%258A%25A4%25E1%2588%258D+%25E1%2588%2598%25E1%2588%258B%25E1%258B%2595%25E1%258A%25AD%25E1%2589%25B5+%25E1%258B%25B5%25E1%258A%2595%25E1%258C%258D%25E1%2588%258D+%25E1%2588%259B%25E1%2588%25AD%25E1%258B%25AB%25E1%2588%259D.jpg" width="320" /></a></div>
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
</div>
<br />
ቤተመቅደስ የገባችበትና መልዓኩ ፋኑኤል በአንድ ክንፉ ህብስትና ፅዋዕ አቅርቦ አንድ ክንፉን ጋርዶ በመመገብ ቤተመቅደስ ቆይታዋ በእግዚአብሔር ፍቃድ መሆኑ የተረጋገጠበት በመሆኑ ታኅሳስ 3 ቀን በየዓመቱ በቤተክርስቲያናችን በደማቅ ሁኔታ ይከበራል።<br />
<br />
በዔሊ ልጆች ኃጥያትና በደል በምርኮ ቆይታ በኃይል ፅዮን ወደ ቤተመቅደስ<br />
እንደተመለሰች ሁሉ አማናዊት ታቦት ቅድስት እመቤታችንም በእናትና አባቷ ቤት ሶስት ዓመት ከኖረች በኋላ ወደ ቤተመቅደስ ገብታለች። « በአታ ለማርያም» ማለት ይኸው ነው ። የማርያም ቤተመቅደስ መግባት ማለት ነው።<br />
እንኳን አደረሳችሁ።</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com1tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-63471437282892693902017-12-02T23:32:00.000+03:002017-12-05T02:19:05.150+03:00ህዳር 24 - ካህናተ ሰማይ<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
ህዳር 24 የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ትልቅ በዓል እንደሆነ ለማታውቁ ወዳጆቼ ፦<br />
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhPeHGKQxM6xbMIPuF3U4OJdB4QEI8DCRAM1t3FsPPAZ0va6UzmJtUW23tV7GKOVGksP-AHP-mAdvYMUYM03WN3LVZBWVT6L1UVolVCSgvan05a89foWyR4O68neA4jNH5_yqEWLaXQ9TY/s1600/tmp_28371-%25E1%258A%25AB%25E1%2588%2585%25E1%258A%2593%25E1%2589%25B0+%25E1%2588%25B0%25E1%2588%259B%25E1%258B%25AD+%25E1%2589%25B0%25E1%258A%25AD%25E1%2588%2588%25E1%2588%2583%25E1%258B%25AD%25E1%2588%259B%25E1%258A%2596%25E1%2589%25B5+%25E1%2588%259B%25E1%258C%25A0%25E1%258A%2595%25E1%2589%25B5+%25E1%2588%25B5%25E1%2588%258B%25E1%2588%25B4+%25E1%258D%2580%25E1%2589%25A3%25E1%258B%2596%25E1%2589%25B5+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC-1326633394.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="1600" data-original-width="900" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhPeHGKQxM6xbMIPuF3U4OJdB4QEI8DCRAM1t3FsPPAZ0va6UzmJtUW23tV7GKOVGksP-AHP-mAdvYMUYM03WN3LVZBWVT6L1UVolVCSgvan05a89foWyR4O68neA4jNH5_yqEWLaXQ9TY/s320/tmp_28371-%25E1%258A%25AB%25E1%2588%2585%25E1%258A%2593%25E1%2589%25B0+%25E1%2588%25B0%25E1%2588%259B%25E1%258B%25AD+%25E1%2589%25B0%25E1%258A%25AD%25E1%2588%2588%25E1%2588%2583%25E1%258B%25AD%25E1%2588%259B%25E1%258A%2596%25E1%2589%25B5+%25E1%2588%259B%25E1%258C%25A0%25E1%258A%2595%25E1%2589%25B5+%25E1%2588%25B5%25E1%2588%258B%25E1%2588%25B4+%25E1%258D%2580%25E1%2589%25A3%25E1%258B%2596%25E1%2589%25B5+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC-1326633394.jpg" width="180" /></a></div>
<br />
ህዳር 24 ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት የስላሴን መንበር ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሃያ አምስተኛ በመሆን ያጠኑበት የመታሰቢያ በዓል ነው፡፡<br />
<br />
ሃያ አራቱ ካህናት ብለን የምንጠራቸው " አኪያል ፣ ቀርቲያል ፣ ደርቲያል ፣ ኤልያል ፣ ዘርቲያል ፣ ቱቲያል ፣ ዮልያል ፣ ከርቲያል ፣ ለብቲያል ፣ ሚታአል ፣ ራዋል ፣ ሳውር ፣ አናዋል ፣ ፈላላአል ፣ አክርቲያል ፣ አፍልኤል<br />
፣ አውኑዋል ፣ ናናንኤል ፣ ዋቲርናናሳኬብኡማስ ፣ ቲታር ፣ ትርሙን ፣ ዝርኬ ፣ እብጦ ፣ አርናስ " ሲሆኑ አባታችንም ሃያ አምስተኛ ሆነው የፀባዖትን ዙፋን ያጠኑ ሲሆን ይኽም በታላቁ ደብረሊባኖስ ገዳም በደማቅ ሁኔታ ይከበራል፡፡ <br />
<a name='more'></a>በዕለቱም አባታችንን በማሰብ ታቦት ወጥቶ ካህናት የአባታችን በረከት ይደርብን እያሉ የገዳሙን ቅፅር እየዞሩ ያጥናሉ፡፡ ያለው ድባብ ልዩ ነው ፤ ከቻላችሁ ወደ ገዳሙ በመሄድ ካልሆነም በየአቅራቢያችሁ ባሉት የአባታችን ደብሮች የጻድቁን በረከት ታገኙ ትካፈሉ ዘንድ እጋብዛለሁ፡፡</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com3tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-32860004028661001142017-11-22T19:27:00.000+03:002017-11-24T00:20:07.977+03:00ዘረኛ አትሁን ፤ በማንነትህ አትታበይ !!<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhbXp0PHLY8CqwVkuu31CCvKYA-y6NAEESiUvGQ6OAJZjNjM6V0A156lYqYYcmWUW4Y2DbFzdjqEjd1j0f3oHa3pupy0xCZGfr0eOHO1EZ53lX0dd8Fr9g4WaL3zlHj6lB0k3WVUdoh6l0/s1600/tmp_30936-%25E1%258B%2598%25E1%2588%25A8%25E1%258A%259B+%25E1%2588%2598%25E1%2589%25B3%25E1%2589%25A0%25E1%258B%25AD+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3+%25E1%258A%25A2%25E1%2589%25B5%25E1%258B%25AE%25E1%258C%25B5%25E1%258B%25AB+%25E1%258B%25A8%25E1%258B%2598%25E1%2588%25AD+%25E1%258C%258D%25E1%258C%25AD%25E1%2589%25B52018894507.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="1158" data-original-width="1600" height="231" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhbXp0PHLY8CqwVkuu31CCvKYA-y6NAEESiUvGQ6OAJZjNjM6V0A156lYqYYcmWUW4Y2DbFzdjqEjd1j0f3oHa3pupy0xCZGfr0eOHO1EZ53lX0dd8Fr9g4WaL3zlHj6lB0k3WVUdoh6l0/s320/tmp_30936-%25E1%258B%2598%25E1%2588%25A8%25E1%258A%259B+%25E1%2588%2598%25E1%2589%25B3%25E1%2589%25A0%25E1%258B%25AD+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3+%25E1%258A%25A2%25E1%2589%25B5%25E1%258B%25AE%25E1%258C%25B5%25E1%258B%25AB+%25E1%258B%25A8%25E1%258B%2598%25E1%2588%25AD+%25E1%258C%258D%25E1%258C%25AD%25E1%2589%25B52018894507.jpg" width="320" /></a></div>
የነገስታት ልጅና ሰመርያ ለምትባለው ሀገር ንጉስ የነበረው 'አክዓብ' በክፋት ተነሳስቶ የድሃውን የናቡቴን የአትክልት ቦታ ለመውሰድ ተመኘ፡፡ ስጠኝ ብሎ ቢጠይቀውም ምስኪኑ ናቡቴ ርስቴንማ አልሰጥህም ብሎ መለሰለት፡፡ በዚህም ንግግር ንጉሱ ተቆጣ በጣም ተበሳጨ፡፡ ሚስቱ ኤልዛቤል ይህን ባየች ጊዜ መሬቱን እንዴት እንደምትወስደው እኔ መፍትሔ አለኝ ብላ በውሸት ወንጀል አስከስሳ የድሃውን የናቡቴን ርስት ቀሙት ፤ ተደብድቦም እንዲገደል አደረጉት፡፡ ብዙም ሳይቆይ ንጉስ አክዓብ እና ሚስቱንም የድሃው የናቡቴ አምላክ እግዚአብሔር ተበቀላቸው፡፡<br />
በማንነህ ወይም በከበሩ ቤተሰቦችህ ወይም በዘር ማንዘሮችህ አትታበይ፣ የአንተ ያልሆነን ባለህ ዕውቀት ፣ ባለህ ገንዘብ ተመክተህ የኔ ካልሆነ አትበል፡፡ አይሁዳውያን የአብርሃም ዘርና ዘመዶች ነን ብለው ሲኮሩና ሲኮፈሱ ጌታችን "የአብርሃም ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ስራ ባደረገችሁ ነበር " ብሎ እንደገሰፃቸው ቅዱስ መፅሐፉ ይነግረናል፡፡<br />
<br />
ብላቴናው ዳዊትን ብንወስድ ከድሆች ወገን የተገኘ እረኛ ነበር፡፡ ነገር ግን በጎነቱና ፃድቅነቱ ከፍ ያለ ክብርን አሰጥተው የከበረ ንጉስ አደረጉት ፡፡ የሰው ልጅ ከምንም ቢነሳ የት መድረስ እንዳለበት የፈጠረው አምላክ ይወስን እንጂ ነገ ምን እንደምንሆን እንኳን የማናውቅ እኛ እንዴት ስለሌላ ለማውራት እንችላለን? ጥቁሩን ነጭ ፤ ነጩን ጥቁር የሚያደርግ ፈራጅ ዳኛ እያለ የኛ እንዲህ መሆን ምን ይባላል?<br />
<br />
<a name='more'></a><br />
ሌሎችን ከድሃ ወይም ከዝቅተኛ ደረጃ ካለው ቤተሰብ በመገኘታቸው እየናቅን ከከበሩ ሰዎች ወገኖች ነን ብለን መመካት ምን ይጠቅመናል? ሁላችን ከአንድ አባት አይደለንም? ወዳጆቼ የሰማያዊ ንጉስ የእግዚአብሔር ልጆች በመሆናችን ምክንያት ፍፁም የከበርን ነን፡፡ እርሱ ለአንዳችን ሳይሆን ለሁላችን አባት ነው፡፡ በስጋ በሀብት በዕውቀት በከበሩ ዘመዶችህ ወይም ዘሮችህ ብትታበይ ግን "እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ. . . የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ፡፡ " ከተባሉት ውስጥ ትሆናለህ፡፡<br />
<br />
እግዚአብሔር 'ሳዖል'ን ከታናሽና ከተናቁት የእስራኤል ጎሳዎች ለእስራኤል ንጉስ አድርጎ እንደመረጠው ይታወቃል፡፡ የተናቀችውን እና የጋለሞታይቱን ልጅ ዮፍታሔን እስራኤልን እንዲመራና ከአሞናውያን እጅ እንዲያድናቸው አድርጓል፡፡ እንዲሁም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን የመረጠው ከልዑላን ፣ ከከበሩ ሰዎች መካከል ሳይሆን ከአሳ አጥማጆችና ካልተማሩ ከምስኪኖች መካከል ነው እንጂ ከጠቢባንና ባለፀጎች ከሆኑት አልነበረም፡፡ ስለዚህ በማንነትህ መታበይና መኩራት ከክርስትና በተቃራኒው መቆም ነው፡፡ የቀደመ መልካም ታሪካችን እና ሀገራዊ ስብዕናችን ዛሬን ሊያሻግረን ካልቻለ ምኑን እኛው ሆንን? ወዳጆቼ ዘር የሚጠቅመው ለእህል ብቻ ነው ፤ ዘረኛ አትሁን!! አትታበይ!!</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-72727266325614855652017-09-26T12:20:00.000+03:002017-12-06T12:34:12.295+03:00እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ ! ... 2010 ዓ.ም<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
</div>
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjkg_ddV3REwegK77X3hX-egsyYtDfdrmiDBFuyknKuVz1Id3dNkaveNFymoEyDHq_48LDgichsuFzTpG225ghR6ww0vAQIpKw8GM1DR7Ro4cNqgXF6Fygd4CeD2nbkvahu_zoKxnljQQc/s1600/tmp_18207-%25E1%2588%2598%25E1%2588%25B5%25E1%2589%2580%25E1%2588%258D+%25E1%2589%25A0%25E1%258B%2593%25E1%2588%258D+%25E1%258B%25B0%25E1%2588%2598%25E1%2588%25AB+%25E1%258A%2595%25E1%258C%258D%25E1%2588%25B5%25E1%2589%25B5+%25E1%258A%25A5%25E1%2588%258C%25E1%258A%2592+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3+%25E1%2588%2598%25E1%2588%25B0%25E1%2589%2580%25E1%2588%258D+%25E1%258A%25A0%25E1%258B%25B0%25E1%2589%25A3%25E1%2589%25A3%25E1%258B%25AD+-1183245977.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="1600" data-original-width="900" height="400" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjkg_ddV3REwegK77X3hX-egsyYtDfdrmiDBFuyknKuVz1Id3dNkaveNFymoEyDHq_48LDgichsuFzTpG225ghR6ww0vAQIpKw8GM1DR7Ro4cNqgXF6Fygd4CeD2nbkvahu_zoKxnljQQc/s400/tmp_18207-%25E1%2588%2598%25E1%2588%25B5%25E1%2589%2580%25E1%2588%258D+%25E1%2589%25A0%25E1%258B%2593%25E1%2588%258D+%25E1%258B%25B0%25E1%2588%2598%25E1%2588%25AB+%25E1%258A%2595%25E1%258C%258D%25E1%2588%25B5%25E1%2589%25B5+%25E1%258A%25A5%25E1%2588%258C%25E1%258A%2592+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3+%25E1%2588%2598%25E1%2588%25B0%25E1%2589%2580%25E1%2588%258D+%25E1%258A%25A0%25E1%258B%25B0%25E1%2589%25A3%25E1%2589%25A3%25E1%258B%25AD+-1183245977.jpg" width="225" /> </a></div>
<div class="separator" style="clear: both; text-align: left;">
ተጨማሪ ለመስቀል በዓል የሰራኋቸውን ምስሎችን ለመመልከት</div>
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
</div>
<a name='more'></a><br />
<img border="0" data-original-height="1600" data-original-width="900" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg8zJRrIKnvKZqWc78ZKijBAgagoIuJ3OiYRjVFCl-6ZtWvyPLqnDBaX5tf8PVc9Fs1WnrXRauIaEFN7U4jHQi51Wdamc0Ej3LsO2t6Yy03mKQqs3rkvDp1WqwPoKjTastg9iOGgfKPnXc/s320/tmp_28207-%25E1%2588%2598%25E1%2588%25B5%25E1%2589%2580%25E1%2588%258D+%25E1%2589%25A0%25E1%258B%2593%25E1%2588%258D+%25E1%258B%25B0%25E1%2588%2598%25E1%2588%25AB+%25E1%258A%2595%25E1%258C%258D%25E1%2588%25B5%25E1%2589%25B5+%25E1%258A%25A5%25E1%2588%258C%25E1%258A%2592+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3+%25E1%2588%2598%25E1%2588%25B0%25E1%2589%2580%25E1%2588%258D+%25E1%258A%25A0%25E1%258B%25B0%25E1%2589%25A3%25E1%2589%25A3%25E1%258B%25AD+3704333390.jpg" width="180" /> <a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiebDtGAzG5VdePvHZIOsAhTvj_80ruNUAxNOXuTJ4HUNqfml-urFRrGdMFNc2xiIwXheWsS1SuR9mDbngSsO2hc41fIcpUKMhNW6aejTgZk_tA3boz6Z1h3ikR64aY8_pflCUk2MeZ-xQ/s1600/tmp_28207-PSX_20170926_062356-1535488250.jpg" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="1600" data-original-width="900" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiebDtGAzG5VdePvHZIOsAhTvj_80ruNUAxNOXuTJ4HUNqfml-urFRrGdMFNc2xiIwXheWsS1SuR9mDbngSsO2hc41fIcpUKMhNW6aejTgZk_tA3boz6Z1h3ikR64aY8_pflCUk2MeZ-xQ/s320/tmp_28207-PSX_20170926_062356-1535488250.jpg" width="180" /></a></div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-53954071903525525352017-09-21T21:38:00.002+03:002017-09-21T21:38:12.917+03:00መስከረም 10፡ ሥዕለ ጸዴንያ ማርያም<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div style="text-align: right;">
<span style="color: red;"><span style="font-family: sans-serif; text-align: left;">ምንጭ፦ የመስከረም አሥር ሰንክሳር እና ተአምረ ማርያም</span> </span> </div>
<br />
ጸዴንያ በምትባል ሀገር ማርታ የምትባል ደግ ሴት ነበረች፡፡ ይህች ደግ ሴት በቤቷ ትልቅ አዳራሽ ሰርታ እንግዶችን እንደ አባታችን አብርሃም<br />
ተቀብላ አብለታ አጠጥታ ማደሪያ ቦታም ሰጥታ ታስተናግድ ነበር፡፡ አባ ቴዎድሮስ የሚባል ኢትዮጵያዊ መነኩሴ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሔድ<br />
መሽቶበት ከማርታ ቤት በእንግድነት አድረ ጠዋት ለመሔድ ሲነሣ ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚሄድ ሲነግራት የእመቤታችንን ሥዕል ገዝተህ<br />
አምጣልኝ ዋጋውን ልስጥህ አለችው፡፡ ገንዘቡን ሥዕሉ ን ሳመጣልሽ ትሰጪኛለሽ ብሏት ሄደ፡፡<br />
<br />
ቅዱሳት ቦታዎችን (መካናትን) ተሳልሞ ሥዕሉን ረስቶ ሳይገዛ ሲመለስ « አደራ ጥብቅ አይደለምን? ያቺ ሴት አደራ ያለችህን ለምን ረሳህ» የሚል<br />
ድምጽ ሰማ ተመልሶ ሄዶ ገዝቶ በረሃ በረሃውን መጓዝ ጀመረ፡፡<br />
በመንገድም እየተጓዘ አንበሳ ሊበላው አየሮጠ ወደ እሱ ሲመጣበት አየ መነኩሴው አንበሳውን ከመፍራት የተነሣ ደነገጠ ተንቀጠቀጠ ደንግጦ<br />
ቁሞ ሳለ ያች ሥዕል ከአንበሳው ጩኸት ሰባት እጅ በሚበልጥ አስፈሪ ድምጽ ጩሃ ተናገረች፡፡ ያን ጊዜ አንበሳው ደንግጦ ፈጥኖ ሸሸ፡፡<br />
መነኩሴውም መንገዱን ቀጠለ፡፡ በመንገዱም ከሚያስፈራ ዱር ውስጥ ወጥተው ወንበዴዎች ሊቀሙትና ሊገድሉት ከበቡት፡፡ ከሥዕለ<br />
ማርያሟም እንደ መብረቅ ያለ ታላቅ ቃል ወጣ ፡፡ ወንበዴዎችም እጅግ ፈርተው ሸሽተው ከጫካው ውስጥ ገቡ፡፡<br />
<br />
ያም መነኩሴ እኝህን የሚያስደንቁ ተአምራት በሰማና ባየ ጊዜ በልቡ « ለእኔ ረዳት ትሆነኝ ዘንድ ወደ ሀገሬ ይዣት እሄዳለሁ እንጂ ለላከችኝ<br />
ሴት አልሰጥም» ብሎ ወደ ሀገሩ ሊሄድ በመርከብ ተሳፈረ፡፡ በባሕር ላይም ሳለ ጽኑ ነፋስ ተነስቶ መርከቡን እየገፋ ማርታ ወዳለችበት<br />
ሀገር ወደ ጼዴንያ ዳርቻ አደረሰው፡፡ ማደሪያም ስለሌለው ወደ ደጓ ሴት ወደ ማርታ ቤት ከእንግዶች ጋር አብሮ ገብቶ አደረ፡፡<br />
<br />
<a name='more'></a><br />
ሲነጋ ወጥቶ ሊሔድ ከደጃፍ ሲደርስ ደጃፉ ጠፍቶት ከአጥሩ ሲታገል ዋለ፡፡ ማርታም «አባቴ ያመመህ የደከመህ ትመስላለህ ዛሬ ደግሞ እዚህ እደርና ነገ<br />
ትሔዳለህ» አለችውና አደረ፡፡ በሁለኛውም ዕለት እንደ መጀመሪያው ቀን በሩን አልፎ መሄድ አቃተውና እዚያው ማርታ ቤት አደረ፡፡ በሦስተኛው<br />
ቀን መውጣት ፈልጐ ከአጥሩ ጋር ሲታገል አይታ «አባቴ የሆንከው ምንድነው እነሆ ዛሬ ሦስተኛ ቀንህ ነው፡፡» አለችው፡፡ መነኩሴውም «<br />
ይህችን ተአምረኛ ሥዕል አልሰጥም ብዬ ነው፡፡ እኔኮ ሥዕል ከኢየሩሳሌም ግዛልኝ ያልሽኝ መነኩሴ ነኝ» ብሎ ሥዕለ ማርያምን<br />
አውጥቶ ሰጣት፡፡<br />
<br />
እርሷም እጅግ በጣም ተደስታ እግዚአብሔርን አመሰገነች፡፡ በሥዕሏም ፊት ሰግዳ ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም<br />
ምስጋናን አቀረበች፡፡ ተቀብላም የተጠቀለለችበትን ልብስ ስትፈታ ፈሳሽ ወዝ ከስዕሊቱ ሲንጠፈጠፍ አገኘች። ከደስታዋም ብዛት የተነሣ የዚያን መነኩሴ እጆቹንና እግሮቹን ሳመች። ከዚህም በኋላ ያቺን ሥዕል ወደ ጸሎት ቤቷ ወስዳ በታላቅ ክብር የምትቀመጥበትን አዘጋጅታ አኖረቻት ማንም<br />
እንዳይዳስሳትም የነሐስን መስኮትን ሰራችላት። በሌሊት የሚያበሩ መቅረዞችን በፊቷ ሰቀለች። ከመቅረዞችም ውጭ የሐር ፡ መጋረጃን<br />
ጋረደች ከሥዕሊቱ እየተንጠፈጠፈ የሚወርደው የወዝ ቅባት የሚጠራቀምበት ከዕብነ በረድ የተሰራ ወጭት አኖረች። ያም መነኮስ<br />
እስከሚሞትበት ቀን ፡ ድረስ ፡ የእመቤታችንን ድንግል ማርያምን ሥዕል እያገለገለ ኖረ።<br />
<br />
የሀገሩም ሊቀ ጳጳሳት የዚያችን ሥዕል ዜና በሰማ ጊዜ ከኤጲስቆጶሳትና ከካህናት ከሕዝቡም ሁሉ ጋር መጣ በሠሌዳም ውስጥ ሆና አገኙዋት<br />
ከዚህ ከአምላካዊ ግብር የተነሣ አደነቁ። ከዚያም ቅባት ቀድተው ለበረከት በተካፈሉ ጊዜ ወዲያውኑ በውጭቱ ውስጥ ይሞላል። ወደ ሌላ<br />
ቦታ ሊወስዷት በፈለጉ ጊዜ ንውጽውጽታ ሁኖ ብዙዎች በድንጋጤ ወደቁ ሥዕሊቱም እስከ ዛሬ በዚያች አገር ትኖራለች። ይህችም ሥዕል ቅዱስ ሉቃስ የሳላት ናት ሥጋ የለበሰች ትመስላለች፡፡ ከፊቷም ወዝ ይንጠባጠባል፡፡ በዚህችም ሥዕለ ብዙ ተአምራት ተደረገ<br />
ሕሙማን ተፈወሱ ዓይነ ስውራን ማየት ቻሉ፡፡<br />
<br />
በዚያ ዘመን የነበረው ሊቀ ጳጳስ ተአምሯን ሰምቶ ሥዕሏ ወደ ማርታ ቤት የገባችበት ዕለት መስከረም 10 ቀን እንዲከበር ሥርዓት ሠራ፡፡<br />
<br />
እግዚአብሔር አምላክ የእመቤታችንን ፍቅሯን በልቦናችን ጣዕሟንባንደበታችን ያሳድርብን። አሜን።<br />
<br />
<br /></div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-51839881259949041592017-09-10T21:38:00.000+03:002017-09-27T21:36:10.715+03:00መልካም አዲስ ዓመት 2010 <div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg6T5UKswAauWogRQelxKkvDqpUomo369LqZ6cFF6FCqFT4sKEtmwK5ZZ_w8GUCpyDHcpMe9RLkj0yp5BQplpWOvVy9EZpHOU41ykrMf0aR6RTXo0zi5ShPxhJSPgDsX_nVdpZxBSWfpyc/s1600/tmp_3333-20170909_170434-701265637.png" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="592" data-original-width="1600" height="118" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg6T5UKswAauWogRQelxKkvDqpUomo369LqZ6cFF6FCqFT4sKEtmwK5ZZ_w8GUCpyDHcpMe9RLkj0yp5BQplpWOvVy9EZpHOU41ykrMf0aR6RTXo0zi5ShPxhJSPgDsX_nVdpZxBSWfpyc/s320/tmp_3333-20170909_170434-701265637.png" width="320" /></a></div>
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEj8Zno1Zr_gvyEUC-ABiF89Lz8_8jtRgOoacMTVJx2FIQMYVgt0_GUGF5ZkaGzCmrJPhK7jZ0hnRV4x1lvN9AckBG6-9oBsh08pYEoD0F8wSRn_9sRM1nvNay5lnVQgFUPn1ZGhbZn7scE/s1600/17+-+1" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" data-original-height="320" data-original-width="180" height="400" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEj8Zno1Zr_gvyEUC-ABiF89Lz8_8jtRgOoacMTVJx2FIQMYVgt0_GUGF5ZkaGzCmrJPhK7jZ0hnRV4x1lvN9AckBG6-9oBsh08pYEoD0F8wSRn_9sRM1nvNay5lnVQgFUPn1ZGhbZn7scE/s400/17+-+1" width="225" /></a></div>
<span id="goog_1733942529"></span><span id="goog_1733942530"></span><br />
<a name='more'></a><br /></div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-46619098322131770992017-04-09T20:52:00.002+03:002017-09-10T21:45:59.414+03:00ሆሳዕና በአርያም <div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div>
<span style="color: #0000ee;">ሰላም ሰላም ውድ ጓደኞቼ እንዴት ከረማችሁ፡፡</span></div>
<div>
<div>
<span style="color: #0000ee;"><br /></span></div>
<div>
<span style="color: #0000ee;">ይኸው እንደተለመደው ለበዓለ ሆሳዕና የመልካም ምኞት መግለጫ </span><span style="color: #0000ee;">ሰርቼ </span><span style="color: #0000ee;">አቀረብኩኝ፡፡</span></div>
<div>
<span style="color: #0000ee;">ከተመቻችሁ ተጠቀሙበት ካሰኛችሁም ለወዳጅ ዘመዶቻችሁ </span><span style="color: #0000ee;">አካፍሉት፡፡</span></div>
<div>
<span style="color: #0000ee;"><br /></span></div>
<div>
<span style="color: #0000ee;">ከፍም አለ ዝቅ.... ሆሳዕናን በደስታ እናክብር</span><span style="color: #0000ee;">፡፡</span></div>
<div>
<br /></div>
</div>
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
</div>
<div style="text-align: left;">
<span style="color: #0000ee;"><br /></span></div>
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgmPWzNkqydl_EP6J6yVyGI6NEPCUB4f_8u5jR4SYT0y_gH0Fx_CTfv8GqJn7flVxUseuDImSd3asaYKxI_omcUUYT5RvaBKrQY1UbRsuYkZh9_Hw_iBWrarocf61rwH7zEjOEhwLkN8lY/s1600/tmp_23705-%25E1%2588%2586%25E1%2588%25B3%25E1%2588%2585%25E1%258A%2593+%25E1%2589%25A0%25E1%258A%25A0%25E1%2588%25AD%25E1%258B%25AB%25E1%2588%259D+%25E1%2588%2586%25E1%2588%25B3%25E1%258B%2595%25E1%258A%2593+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%2589%25A0%25E1%258B%2593%25E1%2588%258D+%25E1%258B%25B5%25E1%2588%25A8%25E1%258C%2588%25E1%258D%2585-1669969741.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="640" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgmPWzNkqydl_EP6J6yVyGI6NEPCUB4f_8u5jR4SYT0y_gH0Fx_CTfv8GqJn7flVxUseuDImSd3asaYKxI_omcUUYT5RvaBKrQY1UbRsuYkZh9_Hw_iBWrarocf61rwH7zEjOEhwLkN8lY/s640/tmp_23705-%25E1%2588%2586%25E1%2588%25B3%25E1%2588%2585%25E1%258A%2593+%25E1%2589%25A0%25E1%258A%25A0%25E1%2588%25AD%25E1%258B%25AB%25E1%2588%259D+%25E1%2588%2586%25E1%2588%25B3%25E1%258B%2595%25E1%258A%2593+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%2589%25A0%25E1%258B%2593%25E1%2588%258D+%25E1%258B%25B5%25E1%2588%25A8%25E1%258C%2588%25E1%258D%2585-1669969741.jpg" width="360" /></a></div>
<br />
<br />
<a name='more'></a><span style="font-family: sans-serif;">መልካም በዓል ይሁንላችሁ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው!!!</span></div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-90256247507649587862017-03-02T20:38:00.002+03:002017-03-02T20:43:15.305+03:00ለአርበኞቻችን፣ ለጀግኖቻችን ያለን ፍቅርና ክብር<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
ለአርበኞቻችን፣ ለጀግኖቻችን ያለንን ፍቅርና ክብር በተግባር ሊገለጽ ይገባል!<br />
<br />
<div style="text-align: right;">
<span style="color: #cc0000;">ፀሐፊ ፦በተረፈ ወርቁ</span></div>
<br />
ኢጣሊያዊው ዕውቅ የታሪክ ጸሐፊና ተመራማሪ ኮንት ሩሲኒ ስለ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ታሪክ በጻፈው ዳጎስ ባለ መጽሐፉ ላይ ስለ አገራችን የረጅም ዘመናት ታሪክና ሥልጣኔ እንዲሁም የነጻነት አኩሪ ተጋድሎ እንዲህ ሲል ነበር የጻፈው፡-<br />
<br />
<div style="text-align: center;">
<span style="color: red;"> <i> What role does fate intend, in the course of future moves within the Dark Continent, for the one African community which has succeeded in remaining free? </i></span><i style="color: red;">More than two thousand years of history, of independence, defended with determination, of wars against everything and everybody are assuredly a great responsibility for a race of human beings to carry.</i></div>
<br />
ይህን የኮንት ሩሲኒ ስለ አገራችን የረጅም ዘመናት የነጻነት ተጋድሎና ታሪክ የሰጠውን ምስክርነት ያስቀደምኩበት ዋናው ምክንያት በዛሬው ጽሑፌ ስለ ጀግኖ አባቶቻችንና እናቶቻችን፣ በተለይም ደግሞ እነዚህ ጀግኖች ባለውለታዎቻችንን የታሪክ ሕያው ዘመናትን ተሻግሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሸጋገር ዘንድ የኢትዮጵያ ጥንታዊት ጀግኖች አርበኞች ማኅበር እያደረገ ባለው ወቅታዊ እንቅስቃሴዎቹ ዙርያ ጥቂት የመወያያ ቁም ነገሮችን በማንሣት እንድንወያይ በማሰብ ነው፡፡<br />
<br />
እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ጥንታዊ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የነጻነት/የአርበኞችን የአልማዝ ኢዮቤልዩ መታሰቢያ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች በታላቅ ድምቀት በአገር አቀፍ ደረጃ ለማክበር ከወዲኹ በታላቅ ዝግጅት ላይ እንደኾነ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ሰምተናል፡፡ ማኅበሩ ከዚህ በዓል ጋር በተያያዘም ለጀግኖች አርበኞቻችን መታሰቢያ የሚኾን ቤተ-መዘክር/ሙዚየም ለማስገንባትም የተንቀሳቃሽ ስልክ አጭር መልእክት የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ እያደረገ ነው፡፡ ከዚህ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ታላቅና በጎ ዓላማ ጎን እንድንቆምም የቴሌ የድጋፍ መልእክት በየዕለቱ እየደረሰን ነው፡፡<br />
<br />
ታዲያስ የኢትዮጵያ ጥንታዊት ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ለዛሬው ክብርና ነጻነት ላበቁን አርበኞቻችን ታሪካቸው ሕያው ሆኖ ከትውልድ ወደ ትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የሚያደርጉትን ጥረት ለማገዝ ምን ያህሎቻችን በተግባር ምላሽ እየሰጠን ይኾን … ብዬ ለመጠየቅ ወደድኹ …?! ዕውቋ አርቲስት እጅጋየሁ ሺባባው/ጂጂ ‹‹ዐድዋ›› በሚለው እጅግ ተወዳጅ ዜማዋ፡-<br />
<br />
<span style="color: red;"> የተሰጠኝ ሕይወት ዛሬ በነጻነት፣</span><br />
<span style="color: red;"> ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ከአጥንት፣</span><br />
<span style="color: red;"> ትናገር ዐድዋ ትናገር አገሬ፣</span><br />
<span style="color: red;"> እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ …! </span>እንድትል በጥዑም ዜማዋ፡፡<br />
<br />
<a name='more'></a><br />
<br />
በእርግጥም መተኪያ የሌላትን፣ ክቡርና ውድ ሕይወታቸውን ሠውተው፣ ደማቸውን አፍሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው፣ ከቅኝ ገዢ ኃይሎች ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ ተናንቀው፣ እናት አገሬ እኛ ልጆችሽ በሕይወት ቆም እያለን የአንቺ ክብር፣ የሕዝቦችሽስ ነጻነት እንዴት ይደፈራል ብለው በዱር በገደል፣ በየተራራውና በየሸንተረሩ በታላቅና አኩሪ ተጋድሎ የአገራችን ነጻነትና ልዑላዊነት ያስከበሩና ታሪክ ስማቸውን በወርቀ ቀለም የከተበላቸውን፣ እነዚህን የምንጊዜም ባለውለታዎቻችን የሆኑት ጀግኖቻችን የሚገባቸውን ክብር አግኝተዋል፣ ሰፊ ዕውቅናም ተችሯቸዋል ብለን በሙሉ አፋችን ለመናገር የምንደፍር ኢትዮጵያውያን ወገኖች ያለን አይመስለኝም፡፡<br />
<br />
<span style="color: red;">ኢትዮጵያ አገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ፣</span><br />
<span style="color: red;"> የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ፡፡ </span>የሚለው ይህ ለብዙዎቻችን ጆሮ እንግዳ ያልኾነ አጭር ስንኝ ለአገራቸውና ለሕዝባቸው ያደረጉት ውለታ የተዘነጋባቸውና ልፋታቸውና ድካማቸው ኹሉ እንደ ከንቱ የተቆጠረባቸው ጀግኖቻችን/አርበኞቻችን የውስጥ ብሶትና ቁጭት የወለደው እንጉርጉሮ ኾኖ ለዘመናት አብሮን የዘለቀ ነው፡፡ ይህን የባለውለታዎቻችንን ብሶትና እንጉርጉሮ፣ ወቀሳና ኀዘን ይበቃ ዘንድ ደግሞ ይህ ትውልድ ትልቅ የታሪክ ሐላፊነትና ሸክም በጫንቃው ላይ ተጥሎበታል፡፡<br />
<br />
አገራችንን ለነጻነትና ለሉዓላዊነት በተደረገ የጦር ሜዳ ውሎ- በጀግንነት፣ በዲፕሎማሲውና በፖለቲካው መስክ፣ በአርቱና በሥነ ጥበብ፣ በስፖርቱና በተሰማሩበት የሙያ መስክ ሁሉ የአገር ባለውለታ የሆኑ፣ የትውልድ አርአያና ተምሳሌት የሆኑ ዕንቁዎቻችንን የሚገባቸውን ክብርና ዕውቅና ልንሰጣቸው ይገባል፡፡ በዚህ ረገድም ከቅርብ ጊዜያት ጀምሮ መንግሥትና አንዳንድ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ለአገርና ለወገን ፍቅርና መቆርቆር ያላቸው ግለሰቦችና ባለሀብቶች የጀመሩትን ለእነዚህ ባለውለታዎቻችን፣ ጀግኖቻችን የሚገባቸውን ክብርና ዕውቅና እንዲያገኙ እያደረጉት ያለውን በጎ እንቅስቃሴ አጠናክረው በተቀናጀ መልኩ ይቀጥሉበት ዘንድ የሚገባ ነው፡፡<br />
<br />
በዚህ ረገድም ጀግኖቻችን፣ ዕንቁዎቻችን የሚገባው ክብርና ዕውቅና ይቸራቸው ዘንድ ሕያው ታሪካቸውና ሥራቸውም ከትውልድ ወደ ትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የኢትዮጵያ ጥንታዊት ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የጀመረውን እንቅስቃሴ በመደገፍና ሁላችንም ከዚህ በጎ ዓላማ ጎን በመቆም የበኩላችንን ጥረት ማድረግ እንዳለብን የሚያጠያይቅ ጉዳይ አይመስለኝም፡፡<br />
የአገራችንና የሕዝቦቻችን ኩራትና ክብር የሆነው የጀግኖቻችን አኩሪ የነጻነት ተጋድሎ ለሕያው ታሪካቸውና ውለታቸው መታሰቢያ የሚሆን ቤተ-መዘክር/ሙዚየም ለማሠራት የጀግኖች አርበኞች ማኅበር እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በሐሳብ፣ በሞራል፣ በሙያ፣ በዕውቀትና በገንዘብ የበኩላችንን ድጋፍ እናደርግ ዘንድ ደጋግሜ አደራ ለማለት እወዳለሁ፡፡<br />
<br />
ይህ የኢትዮጵያ ጥንታዊት አርበኞች ማኅበር የጀመረው ሥራ ከግብ ይደርስ ዘንድ መንግሥት፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ባለሀብቶች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ በኪነ ጥበብና በአርቱ ዙርያ የተሰማሩ፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች፣ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን፣ እንዲሁም ደግሞ የአገራችን የረጅም ዘመን የነጻነት ተጋድሎ ታሪክና ሥልጣኔ ወኔና ጉልበት ሆኗቸው ነጻነታቸው በእኛ እርዳታ የተቀዳጁ የአፍሪካ አገራት፣ ሰላምን በማስክበር ግዴታ- ከሱዳን እስከ ኮንጎ፣ ከሶማሊያ እስከ ላይቤሪያና ኮርያ ልሣነ ምድር ድረስ ለሕዝቦች ነጻነትና ሰላምና ዋጋ የከፈሉ የጀግኖቻችን ባለውለታ የሆኑ የአፍሪካ አገሮች፣ የአፍሪካ ኅብረትና ሌሎችም ወዳጅ አገራት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ በሰፊው የተቀናጀ ቅስቀሳ ሊደረግ ይገባል፡፡<br />
<br />
እስኪ አገራችን ኢትዮጵያና ጀግኖቻችን ለሌሎች አገራትና ሕዝቦች ነጻነትና ልዑላዊነት መከበር የዋሉትን ውለታ በጥቂቱ በማንሳት የዛሬውን መጣጥፌን ልቋጭ፡፡ የዛሬው የ90 ዓመቱ አዛውንት አርበኛ፣ የዚምባቡዌው መሪ ሮበርት ሙጋቤ ለአገራቸው ነጻነትና ለሕዝባቸው መብት በሚታገሉበት በዛን ቀውጢ ወቅት ወታደራዊ ሥልጠና የወሰዱት፣ ድጋፍና ማበረታቻ የተደረገላቸው ከአገራችን ከኢትዮጵያ ነው፡፡ ዚምባቡዌ ነጻነቷን እስክትቀዳጅ ድረስም የአገራችን ደጋፍና እገዛ አልተለያትም ነበር፡፡<br />
<br />
አገራችን ለናሚቢያ ነጻነት በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ቆማ ተሟግታለች፡፡ ለናሚቢያው ስዋፖና ለሞዛምቢኩ ሬናሞ ነጻ አውጪ የአርበኞች ፓርቲ የሬዲዮ ጣቢያቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ ትልቅ ድጋፍ አድርጋለች፡፡ የነጻነት ትግላቸው ፍትሐዊ እንደሆነ በዓለም መድረክ ድምፅዋን ከፍ አድርጋ አሰምታለች፡፡ ለመሆኑ ስንቶቻችን ነን ለኬንያው የነጻት ታጋይ ለሆኑት ለጆሞ ኬንያታ ሴት ልጅ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን በምትከታተልበት ወቅት ትምህርቷን እስክታጠናቅቅ ድረስ በቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ በየወሩ 200 የኬንያ ሽልንግ የገንዘብ ድጎማ ይደረግላት እንደነበር የምናውቀው፡፡<br />
<br />
በተለይም ደግሞ አገራችን ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካ የነጻነት ታጋይ ለኾኑት ለኔልሰን ማንዴላ ወታደራዊ ሥልጠና እንዲያገኙ ከማድረግ ጀምሮ የአፍሪካን ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ እንዲከፈት፣ ለጥቁር ደቡብ አፍሪካ ታጋዮች ከወታደራዊ ሥልጠና ባሻገርም በቀድሞ የቀ.ኃ.ሥ. በአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነጻ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ተመቻችቶላቸው ነበር፡፡<br />
<br />
የደቡብ አፍሪካው የነጻነት ታጋይና የዓለም የሰላም ኖቤል ተሸላሚው ኔልሰን ሮሂላላ ማንዴላ/ታታ ማዲባ <i><span style="color: red;">‹‹Long Walk to Freedom››</span></i> በሚለው ዝነኛ መጽሐፉ ስለ ኢትዮጵያ ጉዞውና ቆይታው በተረከበት ምዕራፉ ላይ ከጠቀሳቸው እውነታዎች መካከል አንድ ሁለቱን ልጥቀስ፡፡<br />
<br />
ወጣቱ የነጻነት ታጋይ ማንዴላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሙሉ በሙሉ በጥቁር ኢትዮጵያውያን አብራሪዎችና የበረራ አስተናጋጆች የሚመራ መሆኑ እጅጉን ያሰገረመውና ያስደነቀው ነገር ነበር፡፡ እርሱና ወገኖቹ በባርነት ቀምበር ውስጥ ወድቀው በሚኖሩባት በአገሩ ደቡብ አፍሪካ እንዲህ ዓይነቱ የአእምሮ ጥበብና ትምህርት የሚጠይቅ ሥራ በነጮች እንጂ በጥቁሮች ሊሠራ እንደማይችል ለዓመታት የተሰበከው የዘረኛው የአፓርታይድ ሥርዓት ስብከት አእምሮውን በርዞት ነበርና ኢትዮጵያውያን ጥቁር ፓይለቶች በተመለከተበት ቅፅበት የዘረኛው የአፓርታይድ መርዘኛ ስብከት ከንቱ መሆኑን ነበር ያረጋገጠው፡፡<br />
<br />
ማንዴላ በዚህ የነጻነታችን ክብርና ኩራት በሆነው በአየር መንገዳችን በቃል ሊገለጽ የማይችል ክብርና ኩራት ነበር የተሰማው፡፡ ማዲባ በዚህ የአርበኞቻችን አኩሪ ተጋድሎ ነጻነታችን ባጎናጸፈው ክብር፣ መደመምና መደነቅ ውስጥ ሆኖ የሚበርበት አውሮፕላን የሱዳንን የአየር ክልል አልፎ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ሲገባ በመስኮቱ አሻግሮ የኢትዮጵያን ተራሮችና ሽንተረሮች በጥልቅ የነጻነት ስሜት ውስጥ ኾኖ በምናብ እንደወጋቸው በዚሁ መጽሐፉ ውስጥ እንዲህ ይተርክልናል፡፡<br />
<br />
እነዚህ ተራሮችና ሸለቆዎች፣ ሜዳና ሸንተረሮች ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አርበኞች ወራሪውን የኢጣሊያን ሰራዊት ያንበረከኩበት፣ እነዚህ ተራሮች በኢትዮጵያን ጀግኖች አባቶቻችን ደምና አጥንት የተዋቡ … ዘመናትን ያስረጁ የነጻነት ተስፋ ጎሕ ያበሰሩ- ሕያው ምስክሮች ናቸው፡፡ በእነዚህ አድማስ ጥግን የነኩ በሚመስሉ ተራሮች ለአፍሪካውያን፣ ለጥቁር ሕዝቦችና ነጻነታቸውን ለሚያፈቅሩ ለሰው ልጆች ኹሉ የተበሰረ የነጻነት ሕያው ድምፅ ገደል ማሚቶ ዛሬም ጎልቶ፣ ደምቆ የሚሰማበት ነው …!!<br />
<br />
እንግዲህ ይህ ከአፍሪካ እስከ አሜሪካ፣ ከአውሮፓ እስከ አውስትራሊያ፣ ከህንድ እስከ ቻይና ተሰማ የኢትዮጵያውያን ጀግኖች አርበኞቻችንን ተጋድሎ፣ ያጎናጸፉንን ክብርና ኩራት በዚህች አጭር ገጽ ለመተረክ የሚታሰብ አይደለም፡፡ የእነዚህ አባቶቻችን ውለታም ፈፅሞ በገንዘብ የሚለካ አይደለም፤ ምክንያቱም ክቡር የሆነው የሰው ሕይወት ነውና የተከፈለበት!!<br />
<br />
እናም በዚህ የደም መሥዋዕትነት የነጻነት አየርን ለመተንፈስ የታደልን እኛ ልጆቻቸው ዛሬ ለጀግኖች አርበኞቻችን ያለንን ክብርና ፍቅር በተግባር ለመግለፅ ሁላችንም ታሪካዊ ግዴታና ሓላፊነት አለብን፡፡ ስለሆነም የእነዚህን ጀግኖቻችንን ሕያው ታሪካቸውንና ገድላቸውን ለትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የኢትዮጵያ ጥንታዊት ጀግኖች አርበኞች ማኅበር- ለጀግኖቻችን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ለማስገነባት ያሰበውን ቤተ-መዘክር ለመገንባት ሁላችንም የበኩላችንን ድጋፍና እገዛ በማድረግ ለባለውለታዎቻችን ያለን ፍቅርና ክብር በተግባር ሊገለጽ ይገባል፡፡ አበቃሁ!!<br />
<br />
<span style="color: red;">ሰላም!!</span><br />
<br />
</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-79026522034057213732017-02-21T21:23:00.002+03:002017-03-02T00:29:59.017+03:00አድዋ ! <div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
ታሪክ የማይሽረው የኢትዮጵያን ድል<br />
እንኳን አደረሳችሁ <br />
<br />
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgW5Wi4DtL9Dr-GLg2Q5TfYQhUkEqM45WcuXCEHGrNH2MRKKofO95j5LINSg8GHdJFHIWbvb92gn-AbS5WIHM0QGaQGLf8vChFgAc2hGtMKne6bf17Ua_hMjyS3QNMncGpptZq6jwKgHQE/s1600/tmp_22878-%25E1%258B%25A8%25E1%258A%25A0%25E1%258B%25B5%25E1%258B%258B+%25E1%258B%25B5%25E1%2588%258D+adwa+victory+-100380672.png" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="165" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgW5Wi4DtL9Dr-GLg2Q5TfYQhUkEqM45WcuXCEHGrNH2MRKKofO95j5LINSg8GHdJFHIWbvb92gn-AbS5WIHM0QGaQGLf8vChFgAc2hGtMKne6bf17Ua_hMjyS3QNMncGpptZq6jwKgHQE/s400/tmp_22878-%25E1%258B%25A8%25E1%258A%25A0%25E1%258B%25B5%25E1%258B%258B+%25E1%258B%25B5%25E1%2588%258D+adwa+victory+-100380672.png" width="400" /></a></div>
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiWqrGWEO17ZXsECGDIIlIfgwj_y6OIsWzK55c-BvgUHXSsNpYorCuzKUL_AKSzy3pWa9wCFqDgrtEMm4EcMGSV2RZXUP5SX1M0GmM5XiHs4_Gh-57rrWYTkP4xt9aACA7GMG_FYGnpRB4/s1600/tmp_20406-20170226_1830501251911333.png" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiWqrGWEO17ZXsECGDIIlIfgwj_y6OIsWzK55c-BvgUHXSsNpYorCuzKUL_AKSzy3pWa9wCFqDgrtEMm4EcMGSV2RZXUP5SX1M0GmM5XiHs4_Gh-57rrWYTkP4xt9aACA7GMG_FYGnpRB4/s320/tmp_20406-20170226_1830501251911333.png" width="191" /></a></div>
<br />
<a name='more'></a><br />
The battle of Adwa<br />
African victory in the age of Empire </div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-25964255050591700102017-02-20T03:12:00.004+03:002017-02-21T21:36:20.091+03:00እንኳን ለሁዳዴ ፆም አደረሳችሁ <div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
እንኳን ለዓብይ (ሁዳዴ) ፆም በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ፡፡<br />
<br />
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEic9GK_okspHbV8zANBXzI8bEvyHsY5vhtwc-MEyE2MT3LDEqpPdTqBKLtFEO1XnMwPHQeBp2Ynylg94i9b6riHhXHRad8VhDTO9B-QA6e6nEKuFCeImqz3rnZEC_Xw1vEat0D8wTEHdR4/s1600/tmp_28592-%25E1%258B%2593%25E1%2589%25A2%25E1%258B%25AD+%25E1%258D%2586%25E1%2588%259D.png-592620785.png" imageanchor="1"><img border="0" height="208" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEic9GK_okspHbV8zANBXzI8bEvyHsY5vhtwc-MEyE2MT3LDEqpPdTqBKLtFEO1XnMwPHQeBp2Ynylg94i9b6riHhXHRad8VhDTO9B-QA6e6nEKuFCeImqz3rnZEC_Xw1vEat0D8wTEHdR4/s320/tmp_28592-%25E1%258B%2593%25E1%2589%25A2%25E1%258B%25AD+%25E1%258D%2586%25E1%2588%259D.png-592620785.png" width="400" /></a></div>
<br />
<a name='more'></a><br />
<br />
መልካም የሱባዔ ጊዜ ይሁንላችሁ !<br />
የካታት 13 , 2009 ዓ.ም<br />
ብስራት ገብሬ</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-70126967454514181062017-01-11T14:19:00.000+03:002017-01-24T01:38:45.746+03:00ከመጥፋቴ ስመለስ<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
ሰላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁና የተወደዳችሁ ወዳጆቼ ፤<br />
<br />
እረጅም ጊዜ ሊባል በሚያስችል ሁኔታ ጥፍት ብዬ እረስታችሁኝ እንደነበር አሰብኩ፡፡ ይህም የሆነው ከዚህ ቀደም እንደገለፅኩት በተለያዩ ምክንያቶች ሲሆን በስራ መደራረብ ፣ በትምህርት ፣ በፊልም ስራ ፣ ወዘተ. .. እንደቀድሞው ቶሎ ቶሎ መገናኘት አልቻልንም፡፡ በዋነኛነት ግን ለረጅም ጊዜ ለመጥፋቴ ምክንያት የሆኑኝን ጉዳዮች ዛሬ ልተንፍስ እና ቀሪውን ደግም ሌላ ጊዜ በሰፊው ማውራት እንችላለን፡፡<br />
<br />
ለዓመታት ሳልማቸው ከነበሩት ትልልቅ ህልም እና ዕቅዶቼ መካከል የ"ፊልም እና ፎቶግራፍ ፕሮዳሽን " ማቋቋም እና የጉዞ ማህበር መመስረት ነበሩ፡፡ በስተመጨረሻም ሁለትና ከዛ በላይ ዓመታት በላይ ፈጅተውብኝ፤ አሁን ግን ሙሉ ለሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ ከግብ ለማድረስ ተችሏል፡፡<br />
<br />
የመጀመሪያው "እይታ ፊልም እና ፎቶግራፍ ፕሮዳክሽን " ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ " እይታ የመንፈሳዊ ጉዞ ማህበር " ናቸው፡፡ ሁለቱንም ለማቋቋምና ስራ ለመጀመር ሳስብ የራሴ አሻራ እንዲኖራቸው ከማሰብ ጀምሮ አብረውኝ እስከሚሰሩት ድረስ በተሻለ ጥንቃቄ ስመርጥ የቆየሁ ሲሆን ቀላል የማይባል ድካም ነበረው ፡፡ ከዛም በላይ ከእናንተ ወዳጆቼ አራርቆኝ ነበር፡፡<br />
<br />
ወደቀደመው መነሻ ስመለስ በብዙ ፈተና ውስጥ ያለፍኩበትና ከአብዛኛዎቻችሁ ጋር ያስተዋወቀኝ " የብስራት እይታ " (www.bisrat-views.blogspot.com) ድረገፅ እንደከዚህ ቀደም ሳይሆን መቀዛቀዝ ይታይበታል፡፡ ይኽም የሆነው ከላይ በገለፅኳቸው ምክንያት ሲሆን በተቻለኝ አቅምም ባለኝ ኃይል ወደቀደመው ተፅዕኖ ፈጣሪነቱና ተነባቢነቱ ለመመለስ እጥራለሁ፡፡ እዚህ ላይ የእናንተም ድጋፍና እርዳታ በጣሙን ያስፈልገኛል፡፡<br />
<br />
በቀደሙት ጊዜያት በጣም የበዙ ፅሑፎች አዘጋጅቼ ሳይወጡ የቀሩ ሲሆን ፤ አንዳንዶቹ በወቅቱ መነበብ የነበረባቸው ናቸው፡፡ ቀሪዎቹን ግን ቀስ እያልኩ አቀርብላችኋለሁ፡፡ አሁንስ እጅህ ከምን ለምትሉኝ እንደመታረቂያ የሚሆኑ በቅርብ ጊዜያቶች ውስጥ የተለያዩ ፅሑፎችን ለእናንተ ወዳጆቼ በእይታ መንፈስ ሃሳቤን በ"ብስራት እይታ " ድረገፅ ላይ አካፍላችኋለሁ፡፡ አርዕስቶቹን ለመዘርዘር ያህል<br />
<br />
* እኔና የሶስት ወሯ ሚስቴ (በተከታታይ ለረጅም ጊዜ)<br />
<br />
* የመንፈሳዊ ጉዞዎች መብዛት ጣጣ<br />
<br />
* ደፋሮቹ አርቲስቶቻችን እና ቤተክርስቲያን<br />
<br />
* ሐዊረ ሕይወት ጉዞ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሩጫ . . .መዝናኛ?<br />
<a name='more'></a><br />
<br />
* አራዶቹ ቄሶች<br />
<br />
* የጋዜጠኞቻችን ምላስ<br />
<br />
* ተከታታይ ድራማዎቻችን<br />
<br />
* ተሐዶሶ በተሐድሶ ሲታደስ<br />
<br />
* ስዕሎቼን ጎብኙልኝ<br />
<br />
* ሕንፃ ቤተክርስቲያኖችን ወዴት?<br />
<br />
* አስራት በኩራታችንን . . . ለማን?<br />
<br />
* የቤተክርስቲያን ጉዳይ እንጂ ማዕበረ ቅዱሳን አይመለከተኝም<br />
<br />
* አዲስ አበባን ለሸገሮች<br />
<br />
እንዲሁም ሌሎች<br />
እናንተ በአድራሻዬ የላካችሁልኝን ሰብስቤ የተሻሉትን ፤ እናንተንም እኔንም የሚመጥኑትን መርጬ አቀርባለሁ፡፡ ሃሳባችሁን አካፍሉኝ፡፡<br />
* * * * * * * * * * * * *<br />
ሀሳቤን ከመቋጨቴ በፊት ቀድሞ ለምታውቁኝ ፣ ለአዲስ ወዳጆቼ እንዲሁም በእኔ ደስስስ ለማይላችሁ እራሴን በድጋሚ ላስተዋውቅ ፡፡<br />
<br />
(ትንሽ ኮፈስ እንደማለት ብዬ) ሙሉ ስሜ ፡ ብስራት ገብሬ እባላለሁ፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ነው የተወለድኩት ፡፡ ጥቂት በማይባሉ ሙያዎች. . .በርታ ተብዬ ተሰይሜ ፣ ተስሜ ፣ ተመርቄ ፣ ተሸልሜ በስራ ላይ እገኛለሁ፡፡<br />
<br />
እንደ ቀድሞው ፓትሪያሪክ የእኔንም ስም ስትጠሩ ከፊት እነዚህን ማስቀደም እንዳትረሱ<br />
ሰዓሊ ፣ ፎቶግራፈር (Photographer )፣ የፊልም ዳይሬክተር እንዲሁም ኤዲተር (Film Director & editor) ፣ የብርሃን የእናቶችና ህፃናት መርጃ ማዕከል መስራች እና የቀድሞ ስራ አስኪያጅ ፣ የሒሳብ ሰራተኛ ፣ አዲስ ድረ-ገፅ ለሚከፍቱ ድርጅቶች አማካሪ ፣ ፀሐፊ (blogger) ፣ ጋዜጠኛ ፣ የንድፍ ሞዴል አውጪ (Graphics Designer ) ፣ የብስራት እይታ ድረገፅ ዋና አዘጋጅ... በቅርቡ ደግም በ M.A ደረጃ በ film production እንግሊዝ ሀገር ለንደን ከተማ በሚገኘው NFTS (National film and television School) ተማሪ፡፡<br />
<br />
ቀደም ባሉት ጊዜያት ደግሞ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ፣ መንፈሳዊ የትምህርት ተቋም ገብቼ ያቋረጥኩ ፣ የበጎ ስራ አድራጎት አምባሳደር እንዲሁም የባንክ ሠራተኛ የነበርኩ አስቂኝ ልጅ ነኝ፡፡<br />
<br />
ምንም ማድረግ አይቻልም ነው ያለው ዲጄው<br />
<br />
<br />
ስለተተዋወቅን ደስስስስስ ብሎኛል፡፡<br />
<br />
በነገራችን ላይ ከላይ ከተዘረዘሩት አርዕስቶች ውስጥ የትኛው ፅሑፍ ቀድሞ ይቅረብላችሁ ? በውስጣችሁ የያዛችሁት ጥያቄ ይኖር ይሆን አካፍሉኝ፡፡<br />
<br />
እፎይይይይ<br />
አመሠግናለሁ ፡፡</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com3tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-54227424839673391842017-01-06T21:54:00.000+03:002017-01-06T21:56:33.371+03:00የገና በዓል አከባበር በላሊበላ<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;"> በዚህ በዓል በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ምዕመናን መንፈሳዊ በዓሉን ለማክበርና በረከት ለመሳተፍ የሚጓዙ ሲሆን ሌሎቹም አብያተ ክርስቲያናቱንና መንፈሳዊ የበዓል ሥርዐቱን ለመጎብኘት ነው። ይህም በዓል ሃይማኖታዊ፣ መንፈሳዊ፣ ትውፊታዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሀገራዊ ፋይዳ አለው።ይህንንም ለማስረገጥ በየዓመቱ ያለማቋረጥ ምዕመናን ከተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች መምጣታቸው ነው።</span><br />
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div align="center" class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif; text-align: center;">
<div class="separator" style="clear: both;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg3ZCEqDH5bN-9t64Om94XBcdbfcNXnMI4QXImxpEi9nyTa7Ksmz6DGgvSuqX-rJiztaeduTuiicGLMgAh7-eBWmP8RodlmPchf8nXP0mAJqQhRe4-on3YpFmfrh8TK0QYkxmO6s2pbOOE/s1600/3.png" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg3ZCEqDH5bN-9t64Om94XBcdbfcNXnMI4QXImxpEi9nyTa7Ksmz6DGgvSuqX-rJiztaeduTuiicGLMgAh7-eBWmP8RodlmPchf8nXP0mAJqQhRe4-on3YpFmfrh8TK0QYkxmO6s2pbOOE/s1600/3.png" /></a></div>
<span style="color: blue; font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"><span style="mso-ignore: vglayout;"></span></span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;">የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በመላው ዓለም የሚከበር ሲሆን በሁሉም የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት፣ ሌሊቱ ማሕሌት ተቁሞ ቅዳሴ እንዳበቃ፣ የበዓል ፍጻሜ ይሆናል፡፡ በላሊበላ ግን በተጨማሪ በዕለቱ ጧት ላይ "ቤዛ ኵሉ" የተሰኘው ክብረ በዓል ከአለት ከተፈለፈሉት የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በአንዱ በቤተ ማርያም ካህናቱ ጋራና መሬት ላይ ሆነው ያከብሩታል፡፡ በተጨማሪ ዕለቱ እራሱ ቅዱስ ላልይበላ(ላሊበላ) ም የተወለደበት<br /><i>በ </i>ታህሣሥ 29 ቀን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልና የገናናው ንጉሥ የቅዱስ ላልይበላ የልደት በዓል በመሆኑም ጭምር በአንድነት በድምቀትና በደስታ ማራኪ በሆነ መንገድ ይከበራል፡፡</span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<br /></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;">የላሊበላው "ቤዛ ኵሉ" አከባበር ትእምርታዊ ነው፡፡ ማሜ ጋራ /ቤዛ ኩሉ ዓለም ሥነ ሥርዓት የሚካሄድበት ቦታ/ ላይ ያሉት የመላእክት ምሳሌ፣ መሬት ላይ ያሉት ደግሞ የእረኞች ምሳሌ ሆነው ዝማሬውን በሆታና በዕልልታ ያጅቡታል፡፡ የክርስቶስ ኢየሱስን መወለድ መጀመሪያ ያወቁ እረኞች በመሆናቸው በአገር ቤት ትውፊቱ እየተነገራቸው የሚያድጉት እረኞች በተለየ ሁኔታ ያከብሩታል፡፡<br />በዓሉ በቦታው አገልጋይ በሆኑ 670 ካህናትና በአካባቢው በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በሚያገለግሉ ከ500 በላይ በሚሆኑ ካህናት ታጅቦ ማህሌቱ ይካሄዳል፤ በዚህ በዓል መላው ነዋሪ ‘ካህን’ የመስሎ ሚታይበት አከባበር ነው፤ የማህሌት ሥነ ሥርዐቱ 2፡30 (ማታ) የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነትና ሌሎች ብጹአን አባቶች በሚገኙበት በየዓመቱ ይከበራል።</span><br />
<a name='more'></a></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;">በዓሉ በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ መከበር የጀመረው ከ900 ዓመት በፊት ነው። ከታህሳስ 23(በዓለ ጊዮርጊስ) ጀምሮ እስከ ዛሬ (ታህሳስ 28) ድረስ ሁሌም 2፡00 ሰዓት ሲሆን የሥርዐተ ማህሌት ደወል ይደወልና በአገልግሎት ይታደራል።</span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;"><br />ይህ በዋዜማው የሚካሄደው የማህሌት ሥርዐት 1፡30 አካባቢ የሚጀመር ሲሆን ልዩ የሚያደርገው የራሱ ቀለምና ዜማ ያለውና ሙሉ ሌሊቱን በወረብ ዝማሬ እየቀረበ የሚታደር መሆኑ ነው።<br /></span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;">ማህሌት ሥነ ሥርዓቱ ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አባታዊ መሪነትና በአስተዳዳሪው አስተባባሪነት እንዲሁም በመሪጌታው በሚመሩ ከ7 ባልበለጡ አስተናጋጆች በሥርዓት ይካሄዳል።የማህሌቱን አካሄድ ስንመለከትም አንድ ጊዜ ከ 12 ያልበለጡ ጥንግ ድርብ የለበሱ' አንድ ጊዜ ደግሞ ከ 12 ያልበለጡ ጥቁር ካባ የለበሱ በድምሩ 24 ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ከቀኝና ከግራ ሆነው በተራ እያሸበሸቡ ያስኬዱታል፡፡</span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
</div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;">ማህሌቱም ማዕጠንት በያዙ 4 ካህናትና ከ8 ያላነሱ ዲያቆናት ወርቅ ካባ ለብሰው፣ የወርቅ አክሊል ደፍተው፣ የወርቅ መስቀል ይዘው መለከት እየነፉ ዙሪያውን በመዞር ማህሌቱን ያጅቡታል። የዚህም ምሳሌነቱ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ መላእክት መለከት እንደሚነፉ ለመግለጥ ሲሆን ለማህሌቱ ትልቅ ድባብ ይፈጥራል። የማዕጠንት ሥርዐቱ ካህናቱ በሊቀ ካህናቱ፤ ዲያቆናቱ በሊቀ ዲያቆኑ ይመራሉ። </span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;"> ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ በአስራ አንዱም ቤተመቅደስ የቅዳሴ ሥርዐት ይፈጸማል። በተለይም ያሉትን ቆራብያን በተቀላጠፈ መልኩ ለማስተናገድ በቤተ ማርያምና በቤተ መድኃኒዓለም በሁለት ልዑክ ቅዳሴው ይከናወናል።</span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
</div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEh6yxr8l6xlAzuLdtx9p0XpJM64lSaRAseqvuoOIYyCuA75a5nDad7Cp1fjGIJUsJ91NgMT8LkTfz-Hi65IT8hGgY_V1rBSxwcszibHPHdC7NY4LZy9YYvDAGL84uL0tF8Im4iR5WbPQLg/s1600/2.png" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEh6yxr8l6xlAzuLdtx9p0XpJM64lSaRAseqvuoOIYyCuA75a5nDad7Cp1fjGIJUsJ91NgMT8LkTfz-Hi65IT8hGgY_V1rBSxwcszibHPHdC7NY4LZy9YYvDAGL84uL0tF8Im4iR5WbPQLg/s1600/2.png" /></a></div>
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;">ከ12፡00 ሰዓት ጀምሮ ጥንግ ድርብ፣ ካባ እንዲሁም ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናት ከአስራ አንዱ ቤተመቅደስ ከእያንዳንዳቸው ከአስራ ሁለት ያላነሱ ካህናት ይህንን ያሬዳዊ ዜማ ለማጀብ ወደ ማሜ ጋራ /ቤዛ ኩሉ ዓለም ሥነ ሥርዓት የሚካሄድበት ቦታ/ ይወጣሉ።</span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div align="center" class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif; text-align: center;">
<span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
</div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
<span style="font-family: "nyala"; font-size: 12pt;">ልክ አንድ ሰዓት ሲሆን ከላይና ከታች የሚሰለፉ ካህናት ቦታቸውን ይይዙና እስከ 4 ሰዓት በሚፈጅ ክንውን እየተቀባበሉ ለሀገር፣ ለወገን፣ ለምድር ሰላም በረከት የሚጸለይበት ‘ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ’ (ዛሬ የዓለም ቤዛ ተወለደ) የተባለው የቀለም ክንውን ይካሄዳል። እንግዲህ የበዓሉን አከባበር በቅዱስ ላልይበላ ልዩ የሚያደርገው አንዱ ይህ “ቤዛ ኩሉ ዓለም” የሚባለው የቀለም ዓይነት ነው።</span><span style="font-family: "times new roman" , "serif"; font-size: 12pt;"></span></div>
<div class="MsoNormal" style="font-family: sans-serif;">
</div>
</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com1tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-68220977309670987202016-12-31T12:53:00.001+03:002016-12-31T12:53:50.134+03:00ታኅሣሥ 22 ፦ ብስራተ ገብርኤል <div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
ታኅሣሥ 22 ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን አምላክን እንደምትወልድ ያበሰረበት መታሰቢያ በዓል፡፡<br />
ልመናዋ ክብሯ በእኛ ለዘላለም በእውነት ይደርብንና አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ያደረገችው ተአምር ይህ ነው፡- ‹‹ልዑል እግዚአብሔር ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ‹ሂድና ለጽዮን ልጅ ለድንግል የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ወደአንቺ መጥቶ ኃይለ ልዑል ወልድ ሥጋሽን ለብሶ ሰው ይሆናል፤ ይኸውም ካንቺ የሚወለደው ጽኑዕ ነው ብለህ ንገራት› አለው፡፡<br />
<br />
‹ደንቆሮዎች የሚሰሙበት፣ ድዳዎቸ የሚናገሩበት፣ ዕውራንም የሚያዩበት፣ ሙታን የሚነሡበት፣ ለምጻሞች የሚነጹበት፣ ሐንካሳዎች የሚሄዱበት፣ በጨለማ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ብርሃን የሚያዩበት ጊዜ እነሆ ደረሰ ብለህ ንገራት› አለው፡፡<br />
ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ በግንባሩ ተደፍቶ ልዑል እግዚአብሔርን<br />
‹ጌታ ሆይ! የምትነግረኝ ይደረግ ዘንድ እንደምን ይሆናል?› አለው፡፡ ጌታም ‹የጀመርኩትን ቸርነት ፈጸምኩ፣ የወይን ግንድ ይቆረጣል (ወልደ እግዚአብሔር ይሞታል)፣ ወይራም ከበለስ ጋር ይተከላል (መስቀል ይተከላል)፣ ቅጽሮችም ይቀጸራሉ (ምግባር ከሃይማኖት ጋር ይሠራል)፣ የኤልፍና የሌሚ ወገን ይነሣል፡፡ ገብርኤል ሆይ! ሄደህ ለዳዊት ልጅ ‹እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ› ብለህ አብሥራት› አለው፡፡ ‹ለዘለዓለም ነግሦ የሚኖረውን እነሆ ትፀንሳለሽ በላት› አለው፡፡<br />
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ሰገደ፡፡ ልብሱንም በላዩ ይዞ በመስቀል ቀኝ ይወርድ ዘንድ ወደደ፡፡<br />
ጌታም ‹መግባትህና መውጣትህ በፍቅር አንድነት ይሁን› አለው፡፡ ‹ዘካርያስን ረግመህ አንደበቱን እንዳሰርህ እርሷን እንዳታሳዝናት ይልቁንም አብዝተህ ደስ አሰኛት አንጂ አለው፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ ደስ እያለው ሊባኖስ ከሚባል ተራራ እስኪሰማ ድረስ ክንፉን እያማታ ወረደ፡፡ በዚህም ጊዜ በዙሪያው ያሉ ሁሉ ‹ይህ የምንሰማው ምንድነው?› ይሉ ነበር፡፡ የተደረገበትንም ቦታ አላወቁትም ነበር፡፡››<br />
<a name='more'></a><br />
<br />
እመቤታችንን በ3 ዓመቷ እናትና አባቷ ብፅዓት አድርገው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋታልና ካህናትም በቤተ መቅደስ ከመካነ ደናግል አስገብተዋት በመልአኩ በቅዱስ ፋኑኤል አማካኝነት ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ እየመጣላት ያንን እየተመገበች ቅዱሳን መላእክት እየጎበኟት 12 ዓመት ኖራለች፡፡ በ15 ዓመቷ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ጌታችንን እንደምትወልድ በዚህች ዕለት አብሥሯታል፡፡<br />
<br />
በመጀመሪያ እመቤታችን ውኃ ቀድታ ስትመለስ የጠተማ ውሻ እያለከለከ ሲመጣ ብታየው ለፍጥረት ሁሉ የምትራራ ናትና በወርቅ ጫማዋ ለዛ ለተጠማው ውሻ ውኃ ስታጠጣ አብሯት የነበሩ ሴቶች ‹‹ማድጋሽን አጎደልሺው፣ ቀድቼ እሞለዋለሁ እንዳትይ ጉድጓዱ ጥልቅ ነው መቅጃም የለሽም›› አሏት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ‹‹ውሃ የሚገኘው ከወደላይ ነው እንጂ ከወደታች ነውን? ፍጥረቱን ያጠጣ ጌታ ይሞላልኛል›› አለቻቸው፡፡<br />
<br />
ማድጋዋም በተአምራት ሞልቶ ተገኘ፡፡ ሴቶቹም ዳግመኛ ‹‹በዚህ ዘመን አምላክ ከድንግል ይወለዳል ይላሉ ካንቺ ይሆን?›› እያሉ ሲዘብቱባት ወዲያው ከወደኋላዋ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ዞር ብትል የተናገራትን አጣችው፡፡ በዚህም ጊዜ ‹‹አባቴን አዳምን እናቴን ሔዋንን ያሳተ ጠላት ይሆናል›› ብላ ሄደች፡፡<br />
ዳግመኛም እመቤታችን ከቤት ደርሳ ማድጋዋን ስታስቀምጥ መልአኩ አሁንም በድምፅ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹ምነው ይህስ ነገር ደጋገመኝ እንዲህ ያለውን ነገር ቤተ መቅደስ ሄደው ሊረዱት ይገባል›› ብላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዳ ወርቅና ሐር እያስማማች ስትፈት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እሁድ ቀን በ3 ሰዓት በገሃድ ተገለጸላትና እጅ እየነሳ እየሰገደ አበሠራት፡፡<br />
‹‹የዕውነተኛ ንጉሥ እናቱ እመቤታችን ላንቺ ፍቅር አንድነት ይገባል›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹አንቺ ከሴቶች ይልቅ ተለይተሸ ንዕድ ክብርት ነሽ›› አላት፡፡ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናቸ ክብርት እመቤታችንም የብርሃናዊውን መአልክ የቅዱስ ገብርኤልን ቃል በሰማች ጊዜ<br />
‹‹እንዲህ ያለውን ሰላምታ እንደምን ይቀበሏል/ እንዴትስ መቀበል ይቻላል? እንጃ›› አለችው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ‹‹ማርያም ሆይ! መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል፣ ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ይለብሳልና አይዞሽ አትፍሪ›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህ ካንቺ የሚወለደው ጽኑ ከሃሊ ነው፡፡ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ፣ እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፣ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፣ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም›› አላት፡፡<br />
<br />
እመቤታችንም መልአኩን ‹‹ምድር ያለ ዘር ፍሬን አትሰጥምና እኔ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?›› አለችው፡፡ መልአኩም መልሶ ‹‹መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ እርሷ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፡፡ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፣ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና›› አላት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› አለችው፡፡<br />
መልአኩም ከእርሷ ዘንድ ሄዶ ተሠወረ፡፡ አካላዊ ቃልም በማኅፀኗ አደረ፡፡ በዚያችም ቅጽበት የእመቤታችን የፊቷ መልክ ተለወጠ፣ እንደፀሐይም አሸበረቀ፡፡ ልመነዋ ክብሯ እኛ ለዘለዓለም በዕውነት ይደርብን፡፡<br />
<div>
<br /></div>
</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-49690098916839696712016-02-24T12:51:00.000+03:002017-02-23T23:49:38.793+03:00የካቲት 16 " ኪዳነ ምህረት<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃልኪዳን ማለት ነው፡፡በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው፡፡<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEisjCAv41zCUtF7kW6MRslebwv4Yq-yW5xM-aYaLs-m5x51_2IwcpEzt47xmMshY8jFodjnEcUc1G9iDgPlGYaFzqmHGNOaVJ94G4ecwKlsAS4t5cLYE7cbhbzxCUYdcZLHVfi2iU-VZAk/s1600/tmp_30719-%25E1%258A%25AA%25E1%258B%25B3%25E1%258A%2590+%25E1%2588%259D%25E1%2588%2585%25E1%2588%25A8%25E1%2589%25B5+16+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC-1522100030.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="225" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEisjCAv41zCUtF7kW6MRslebwv4Yq-yW5xM-aYaLs-m5x51_2IwcpEzt47xmMshY8jFodjnEcUc1G9iDgPlGYaFzqmHGNOaVJ94G4ecwKlsAS4t5cLYE7cbhbzxCUYdcZLHVfi2iU-VZAk/s400/tmp_30719-%25E1%258A%25AA%25E1%258B%25B3%25E1%258A%2590+%25E1%2588%259D%25E1%2588%2585%25E1%2588%25A8%25E1%2589%25B5+16+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC-1522100030.jpg" width="400" /></a></div>
<br />
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ ክርስቶስ መካነ መቃብር ጎለጎታ እየወረደች ትፀልይ ነበር፡፡ ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችው ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ የምህረት ቃል ኪዳን ገባለት ፡፡<br />
<br />
እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ፣ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ ቃልኪዳን አደረገ፡፡<br />
« ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ። … » መዝ, 89 : 3 እንዲል መፅሐፉ፡፡<br />
<br />
ስሟን ለሚጠሩ፣ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ቃልኪዳን ሰጥቷታል ፡፡<br />
<br />
ታላቁ መፅሐፍ እንዲህ ይላል፦<br />
". . . ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ። " ኦሪት ዘፍ. 9 : 16<br />
<br />
በዚህም መሠረት ቃልኪዳኗን ምክንያት በማድረግ ኪዳነ-ምህረት እያልን እንጠራታለን!<br />
<br />
እንኳን ለ«ኪዳነምህረት» አደረሳችሁ። የእመቤታችን ምህረት እና ረድዔት፤በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com1tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-41827546783499276922016-02-22T01:07:00.001+03:002016-02-22T01:12:18.108+03:00እንኳን ለፆመ ነነዌ አደረሳችሁ<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
እንኳን ለፆመ ነነዌ አደረሳችሁ። የነነዌን ህዝብ ለቅሶና እንባ ተመልክቶ ፊቱን ከቁጣ የመለሰ አምላክ የእኛንም ሀጢያትና ክፋት ከምንም ሳይቆጥር ፀሎት እና ልመናችንን ሰምቶ ይቅር ይለን ዘንድ እመኛለሁ።<br />
መልካም የፆም ቀናት ይሁንላችሁ!<br />
<br />
<div style="text-align: center;">
* * * * *</div>
<br />
ዮናስም ተነሥቶ እንደ እግዚአብሔር ቃል ወደ ነነዌ ሄደ፤ ነነዌም የሦስት ቀን መንገድ ያህል እጅግ ታላቅ ከተማ ነበረች። ዮናስም የአንድ ቀን መንገድ ያህል ወደ ከተማይቱ ውስጥ ሊገባ ጀመረ፤ ጮኾም። በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች አለ። የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ፤ ለጾም አዋጅ ነገሩ፥ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ። ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፤ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ። አዋጅም አስነገረ፥ በነነዌም ውስጥ የንጉሡንና የመኳንንቱን ትእዛዝ አሳወጀ፥ እንዲህም አለ። ሰዎችና እንስሶች ላሞችና በጎች አንዳችን አይቅመሱ፤ አይሰማሩም ውኃንም አይጠጡ፤<br />
<a name='more'></a>ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ፥ ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩኹ፤ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ። እኛ እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደ ሆነ፥ ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?<br />
<br />
<div style="text-align: right;">
<span style="color: #cc0000;">ትንቢተ ዮናስ 3 ፥ 4 - 9</span></div>
</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com2tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-25210137211501675392016-01-07T22:47:00.000+03:002016-01-11T13:30:33.951+03:00እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ <div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgkTNpwZG9qhqtKem0DtPRo_jz0Pd_esPA2ea-6G3kS3eKUHCiHopf9g_ULuAbQz0Vjt439le9v3CFFA0B8An7XJvhtl0JG1mfAWXj0BSypZTw694kNPMumqnWpfcIk2AG9BAfZyyBJSb8/s1600/%25E1%258A%25A5%25E1%258A%2595%25E1%258A%25B3%25E1%258A%2595+%25E1%258A%25A0%25E1%258B%25B0%25E1%2588%25A8%25E1%2588%25B3%25E1%2589%25BD%25E1%2588%2581+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3.jpg" imageanchor="1" style="clear: left; float: left; margin-bottom: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="400" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEgkTNpwZG9qhqtKem0DtPRo_jz0Pd_esPA2ea-6G3kS3eKUHCiHopf9g_ULuAbQz0Vjt439le9v3CFFA0B8An7XJvhtl0JG1mfAWXj0BSypZTw694kNPMumqnWpfcIk2AG9BAfZyyBJSb8/s400/%25E1%258A%25A5%25E1%258A%2595%25E1%258A%25B3%25E1%258A%2595+%25E1%258A%25A0%25E1%258B%25B0%25E1%2588%25A8%25E1%2588%25B3%25E1%2589%25BD%25E1%2588%2581+%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25B5%25E1%2588%25AB%25E1%2589%25B5+%25E1%258C%2588%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25AC+%25E1%258A%25A5%25E1%258B%25AD%25E1%2589%25B3.jpg" width="225" /></a></div>
የአለም መድኀኒት ጌታ ዛሬ ተወለደ !! መድኀኒት ክርስቶስ ፤ የተዋረደውን ማንነታችንን ሊያከብር ፣ የተጎሳቆለውን ፀጋችንን ሊያድስ ፣ ከተጣልንበት በክብር ሊያነሳን ፣ የልጅነት ስማችንን ሊመልስ፣<br />
<br />
"አባ...አባት ! ብለን የምንጠራበት መንፈስ ሊሰጠን ትንቢት አስነግሮ ... ቀን ቆጥሮ ቀን አስቆጥሮ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ስጋ እና ነፍስ ነስቶ በድንቅ የተዋህዶ ሚስጢር ተወለደ ፡፡ ዕለቱም ዛሬ ነው !!<br />
<br />
ሰብዓሰገል ስጦታን ያመጡልህ ፣ እረኞች ከመላዕክት ጋር ያመሰገኑህ ፣ እንስሳት ትንፋሻቸውን የገበሩልህ የቤተልሔሙ ጌታ ሆይ ክብርና ምስጋና ላንተ ይሁን ፡፡<br />
<br />
<a name='more'></a><br />
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ፡፡<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<br /></div>
</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-36015960677639603542015-10-24T07:16:00.000+03:002015-11-23T17:19:26.043+03:00የኢትዮጵያን ጥንታዊ ታሪክ ከአራት ሺሕ ዓመታት የሚያዘልለው ግኝት<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div style="text-align: right;">
በ ሔኖክ ያሬድ</div>
<br />
<br />
<span style="font-size: small;"><b><span style="font-size: medium;">ጥንታዊው የኢትዮጵያ ታሪክ ሲነሳ ‹‹የሦስት ሺሕ ዓመት››</span></b></span><br />
<span style="font-size: small;"><b><span style="font-size: medium;">የሚለው ጎልቶ ይሰማል፡፡ የሥልጣኔው መንደርደሪያ ከአክሱም</span></b></span><br />
<span style="font-size: small;"><b><span style="font-size: medium;">ዘመን ሲያልፍም የይሓ እና የደአማት ሥርወ መንግሥትም</span></b></span><br />
<b><span style="font-size: small;">ይጠቀሳሉ፡</span><span style="font-size: large;">፡</span></b><br />
<br />
ከሦስት ሺሕ ዘመን ጋርም የንግሥተ ሳባና የልጇ ቀዳማዊ ምኒልክ ታሪክ<br />
ይነሳል፡፡ በምሥራቅ ትግራይ የቀድሞው ዓጋመ አውራጃ ዋና ከተማ<br />
ዓዲግራት በሰሜን አቅጣጫ 8 ኪሎ ሜትር ተሂዶ የሚገኘው የጉለ<br />
መኸዳ ወረዳ ከቀዳሚቷ ንግሥት ጋር የሚያያዝ ታሪክ አለው፡፡ ንግሥቲቱ<br />
በኢትዮጵያ ታሪክ ሦስት ዓይነት ስም ሳባ፣ ማክዳ እና አዜብ አላት፡፡<br />
የወረዳው መጠሪያ ‹‹ጉለ መኸዳ›› ከማክዳ ጋር ሲያያዝ ‹‹ጉለ›› (ጐል)<br />
የሚለው ቃልም በረት የሚል ትርጉም እንዳለው ይነገራል፡፡ ከሳባ ጋር<br />
የተያያዘው ስምም ሶበያ በሚባል የሚጠራውና በወረዳው ውስጥ<br />
የሚገኘው ጥንታዊ ስፍራ ነው፡፡<br />
<br />
ከ43 ዓመት በፊት በጉለ መኸዳ አካባቢ ጥናት ያደረገው ፈረንሣዊው<br />
አንፍረይ፣ ባገኛቸው መረጃዎች መሠረት ከሦስት ሺሕ ዓመት በፊት<br />
አካባቢው ሰዎች ይኖሩበት እንደነበር ገልጿል፡፡<br />
በቀጣይ ጥናትና ምርምር የሚደገፍ ቢሆንም ንግሥተ ሳባ በዚህ አካባቢ<br />
ትኖር እንደነበረ ለመረዳት አያዳግትም ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች፡፡<br />
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጉሎ መኸዳ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ሥልጣኔ<br />
የሚያመለክቱ በርካታ ቅርሶች እየተገኙበት ነው፡፡ የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ<br />
ሌክቸረሩ አቶ ሐጎስ ገብረማርያም እንደሚገልጹት፣ ከ10 ዓመት በፊት<br />
የጉለ መኸዳን ኦርኪዮሎጂካዊ ሀብቶችም ሕቡዕ ምሥጢር አስመልክቶ<br />
ለሁለት ዓመት ዳሰሳና ጥናት ተካሂዶ ነበር፡፡<br />
<br />
<a name='more'></a><br />
<br />
ጥናቱ የምሥራቅ ትግራይ አርኪኦሎጂ ፕሮጀክት የሚባል ሲሆን፣<br />
መቀመጫውን በካናዳ ባደረገው ሳይመን ፍሬሰር ዩኒቨርሲቲ የሚደገፍና<br />
በዩኒቨርሲቲው የአርኪዮሎጂ ፕሮፌሰር ካትሪን ዲአንድሪያ የሚመራ<br />
ነው፡፡ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በመስቀል በዓል አጋጣሚ ባዘጋጀው<br />
ሁለተኛው የአርኪዮሎጂ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የጉለ መኸዳ አዳዲስ<br />
ግኝቶችን የተመለከተ ጥናት በፕሮፌሰሯ ቀርቦ ነበር፡፡<br />
እንደ ፕሮፌሰር ካትሪን ማብራሪያ የሁለት ዓመቱ ዳሰሳዊ ጥናት<br />
ከተጠናቀቀ በኋላ በቀጥታ የተገባው ወደ ቁፋሮ ነበር፡፡ የመጀመሪያው<br />
ቁፋሮ የተካሄደበት ቦታ የተመረጠው መዝበር ከአክሱም ሥልጣኔ በፊት<br />
የነበረን ከተማ የሚያመላክት ፍርስራሽ ሕንፃ ስለተገኘበት ነው፡፡ ይህም<br />
ከተማ ከክርስቶስ ልደት በፊት 800 ዓመት ላይ የነበረ መሆኑ<br />
ተረጋግጧል፡፡ ሁለተኛው ቁፋሮ የተካሄደበት ቦታ ዖና ዓዲ የሚባልና<br />
በሸዊት ለምለም ቀበሌ መነበይቲ መንደር የሚገኝ ነው፡፡<br />
መነበይቲን ከመዝበር የሚለየው ከአክሱም ሥልጣኔ በፊትና በዘመነ<br />
አክሱም መካከል መኖሩ ነው፡፡ እንደ ፕሮፌሰር ካትሪን ማብራሪያ<br />
መዝበር ጥንታዊ ማዕከል ሲሆን፣ መነበይቲና አካባቢው ደግሞ<br />
ከአክሱም ሥልጣኔ ጋር የሚያመሳስለው ቅሪቶችን ይዞ መገኘቱ ነው፡፡<br />
በዋናነት በመዝበር የተካሄደው ጥናት እጅግ ጥንታዊና በጊዜው<br />
የነበረውን ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊን ይዞታ ምን<br />
ይመስል እንደነበር ምላሽ የሚሰጥ ነው፡፡<br />
<br />
<b>መዝበር</b><br />
<br />
በጻሕዋ አካባቢ የሚገኝና ለአምስት ዓመት ያህል ቁፋሮ የተካሄደበት<br />
ስፍራ ነው፡፡ ግኝቱም የሚያሳየው በአክሱም ሥልጣኔ በፊት ከክርስቶስ<br />
ልደት 1000 – 1500 ዓመት በፊት ታላቅ ማዕከል ሆኖ መኖሩ ነው፡፡<br />
በኢትዮጵያ ትልቅ ቦታ ካለው ከይሓም ከ400 እስከ 450 ዓመት በፊት<br />
እንደሚቀድም መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በመዝበር ረዥም ዕድሜ<br />
ያስቆጠረ ሥልጣኔ እንደነበረም ተረጋግጧል፡፡ ይህም ከደቡብ ዓረቢያ<br />
የፈለሱ ሰዎች ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት የነበረ<br />
ሥልጣኔ መሆኑን መረጋገጡን ፕሮፌሰር ካትሪን ገልጸዋል፡፡<br />
እንደ ፕሮፌሰሯ አገላለጽ፣ ቀደም ሲል የአርኪዮሎጂ ተመራማሪዎች<br />
ጥንታዊ የኢትዮጵያ ሥልጣኔ መነሻን ከዓረብ ከፈለሱ ሰዎች ጋር የተያያዘ<br />
ነው የሚለው እምነታቸው ትክክል አለመሆኑን ኢትዮጵያውያን የራሳቸው<br />
ጥንታዊ ሥልጣኔ እንደነበራቸው በመዝበር የተገኘው መረጃ<br />
አረጋግጧል፡፡ የመዝበር ሥልጣኔ ፍልሰተኞች ከመምጣታቸው 800<br />
ዓመታት በፊት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ሲሉም አስምረውበታል፡፡<br />
ሌሎቹ ግኝቶች በዘመኑ የተላመዱ የቤት እንስሳት እነ በግ፣ ግመል፣<br />
ፍየል፣ ውሻ፣ አህያ፣ እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ የተሟላ መረጃ የያዘ<br />
የዶሮ ቅሪተ አካል በዚሁ ስፍራ መገኘቱም ተጠቁሟል፡፡ ለተለያዩ<br />
አገልግሎቶች የሚውሉ ጥንታዊ የድንጋይ መሣርያዎችም መገኘታቸው<br />
የዘመኑን ዕደ ጥበብና ሥነ ጥበብ ምን ያህል እንደነበርም ተመራማሪዋ<br />
አመልክተዋል፡፡<br />
<br />
<b>ዖና ዓዲ (መነበይቲ</b>)<br />
<br />
መነበይቲ ከአዲስ አበባ 916 ኪሎ ሜትር ግድም የምትገኝ ከፋፂ ወደ<br />
ዛላምበሳ በሚወስደው አውራ ጎዳና በምሥራቅ አቅጣጫ ተገንጥሎ<br />
ሁለት ኪሎ ሜትር ተጉዞ የሚገኝ ስፍራ ነው፡፡<br />
በአፈ ታሪክ የንግሥተ ሳባ ጥንታዊ ቤተ መንግሥት የሚገኝበት፣<br />
ቀዳማዊ ምኒልክ ማይበላ (አስመራ አካባቢ) ከተወለደ በኋላ ወደዚህ<br />
ቤተ መንግሥት መምጣቱና ማደጉ ይነገራል፡፡ የመንደሩ ነዋሪ የሆኑት<br />
ቄስ ገብረ ሕይወት ምኒልክ እዚህ ቦታ እንዳገሩ ባህል ቃርሳ<br />
እየተጫወተ ማደጉን ወላጆቻችን ያቆዩልን ታሪክ ነው ይላሉ፡፡<br />
በመነበይቲ በቁፋሮ የተገኙት የሕንፃ ፍራሾች፣ የሸክላ ሥራዎች፣ የሰውና<br />
የእንስሳት ቅሪተ አካል ቅድመ አክሱምና በዘመነ አክሱም የነበሩ<br />
መሆናቸውም ተመልክቷል፡፡<br />
የመነበይቲ ቁፋሮ ተጀመረ እንጂ አልተገባደደም የሚሉት ፕሮፌሰር<br />
ካትሪን ለሦስት ዓመት የተከናወነው ቁፋሮ ተጨማሪ ሰባት ዓመታት<br />
ያስፈልገዋል፡፡ በመነበይቲ እየተካሄደ ያለው ቁፋሮ ለበርካታ ጥያቄዎች<br />
ምላሽ እንደሚሰጥ፣ ይህም የአክሱም ሥልጣኔ ገንኖ በነበረበት ጊዜ<br />
በመነበይቲ የነበረው የንግድ እንቅስቃሴ ምን ይመስል እንደነበር፣ ራሱን<br />
ችሎ ነው ወይስ ከሌሎች ጋር ተሳስሮ ነው የሚለው ወደፊት የሚታይg<br />
ነው፡፡<br />
እንደ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዓለም መብርሃቱ<br />
አገላለጽ፣ የትግራይ አካባቢ የሃይማኖቶች ሁሉ መጀመሪያ፣<br />
የሥልጣኔዎችም ከይሓና ከአክሱም ጀምሮ የሚታወቅ ነው፡፡ በዋናነት<br />
ደግሞ መነበይቲ የንግሥት ማክዳ (ሳባ) የቅድመ የሓ የቅድመ አክሱም<br />
ቤተ መንግሥት እንደነበረ የካናዳ ፕሮፌሰሮች ከኢትዮጵያውያን ምሁራን<br />
ጋር ሆነው እየሠሩት ያለው ጥናት እንዲሁም በመነበይቲ የተገኘው<br />
የንግሥት ማክዳ ቤተ መንግሥት ፍራሽ የኢትዮጵያን ታሪክ በአንድ<br />
ዕርምጃ ወደፊት የሚወስድ መሆኑን አመልክተዋል፡፡<br />
በመዝበርም ሆነ በተለያዩ አካባቢዎች የተገኙ ልዩ ልዩ ቅርሶችን<br />
የሚቀመጡበት ሙዚየም ለማስገንባት እንቅስቃሴ የተጀመረ መሆኑንና<br />
የዓዲግራት ከተማ አስተዳደርም ለሙዚየሙ መገንቢያ የሚፈለገውን<br />
ያህል መሬት ለመስጠት በዓለም አቀፍ ጉባኤው ማጠቃለያ ላይ ቃል<br />
ገብቷል፡፡</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-15247428434838187272015-10-01T07:41:00.001+03:002015-10-01T22:01:46.888+03:00ይድረስ ለ ‹‹ ባላገሩ ምርጥ ››<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjhOHJvdlfLGgs0-FV6jItyR0XaUnSK69weqpFXPhMrIFpPbMNOr6cgcDrciWhHqcjmHGq9d6x7_z5ppAkbw_9uI-6BDv6ONIcaFpj74WJSiFjV9JAKV_OnPMgAD7jpfC6-M5DF92tjuyI/s1600/PSX_20151001_050528.jpg" imageanchor="1" style="clear: left; float: left; margin-bottom: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjhOHJvdlfLGgs0-FV6jItyR0XaUnSK69weqpFXPhMrIFpPbMNOr6cgcDrciWhHqcjmHGq9d6x7_z5ppAkbw_9uI-6BDv6ONIcaFpj74WJSiFjV9JAKV_OnPMgAD7jpfC6-M5DF92tjuyI/s320/PSX_20151001_050528.jpg" width="233" /></a></div>
የባላገሩ ምርጥ ውድድር ከተጀመረ ከዓመታት ቆይታ በኋላ መስከረም 17 , 2008 በመስቀል በዓል ዕለት መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡ የውድድሩ መርዘምና አላልቅ ማለት የሆነ ወቅት ላይ አጀብ አሰኝቶ የነበረ ቢሆንም ወደ ማለቂያው አካባቢ ግን የብዙዎችን ቀልብ መሳብ ችሎ ነበር ፡፡ በተለይ የመጨረሻዎቹ 25 ተወዳዳሪዎች ሲቀሩ ብዙ ደስ የሚሉ ነገሮችን ማየት ችለናል፡፡ እኔም ባገኘሁት አጋጣሚ ማየት የጀመርኩት በዚህ ወቅት ነበር ፡፡<br />
'ባላገሩ ምርጥ' በሀገራችን ቀደም ብለው ከታዩ እና አሁንም እየታዩ ከሚገኙ የድምፅና የዳንስ ውድድሮች በብዙ ነገሩ የተሻለ ሲሆን ለንፅፅርም የማይበቃ በከፍተኛ በጀት የሚሰራ መሆኑ ያስታውቃል፡፡ በዚህም ምክንያት ስነውበቱን እና ኪነጥበባዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ለዓመታት መዝለቅ ችሏል፡፡ ቢሆንም ምንያህል ልፋት እንደሚጠይቅ እንዲሁም ምን ያህል ሊያደክም እንደሚችል ማሰብ ቀላል ነው፡፡ እጅግ ብዙ እየተለፋበት እንደሚሰራ እና አዘጋጆቹም ጠንካሮች እንደሆኑ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ጊዜያቶች በሄዱ ቁጥር የውድድሩ ጥራት እየጨመረ እየጨመረ መሄድ መቻሉን የሚነግረን ነገር ስላለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ በተወሰነ መልኩ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የባለሙያ እጥረቶች እንዳሉ ቢታይም ሁልጊዜም መሻሻሎች ነበሩት፡፡ ይህም ባላገሩ ምርጥን ምርጥ ያሰኘዋል፡፡<br />
<br />
<div style="text-align: center;">
<span style="color: blue; font-size: x-large;"> ኢትዮጵያዊነትን መውደድ</span></div>
<br />
ባላገሩ ምርጥን እንድመለከት ካደረጉኝ ጉዳዮች ዋነኛው ኢትዮጵያዊነት ላይ ስለሚያተኩር እና ስለሚያውጠነጥን ነው፡፡<br />
እስከመጨረሻ ይህን ዓላማ ይዞ መዝለቅ መቻሉ ደግሞ አስደሳች ነበር ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ትልልቅ ሃሳቦችን አንግበው በቅርብ ቀን ጠብቁን ብለው ደስኩረው ትዕይንቱ ወይም ፕሮግራሙ ሲጀመር ደግሞ ምንም ዓይነት ሀገራዊ ለዛ እና ሀገራዊ ጥፍጥና የሌለው አቀራረቡም ፣ ይዘታቸውም ባህር ማዶ ናፋቂነትን ሰባኪ ሆኖ የሚቀርቡ የቴሌቪዥን 'ፕሮግራሞች በሞሉባት ሀገርእንደ ባላገሩ አይነትን ማበረታታት ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ <br />
<a name='more'></a><br />
ባላገሩ ምርጥ ሲጀምርም ባላገሩ 'አይዶል (idol)' ብሎ ነበር፡፡ በወቅቱ አይዶል (idol)'የሚለውን ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ቃል እንዴት ‹‹ ባላገሩ ›› ከሚለው ውብ ሀገርኛ ቃል ጋር እንዴት ሊዛመድ ይችላል ብዬ ጠይቄ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ ዘግይቶም ቢሆን ግን ለማስተካከል ሞክረዋል፡፡ከ ‹‹ባላገሩ አይዶል›› ወደ ‹‹ባላገሩ ምርጥ ››፡፡ በዛ ላይ ‹ አይዶል› የሚለውን ቃል ‹ ምርጥ › ወደሚል ቃል ለመለወጥእና ለመቀየር የተጠቀሙበት ዘዴ ብልሃትን ከብልጠት ጋር አዋህዶ ውበት በታከለበት መልኩ ነበር፡፡ይህም ለዓመታት በተመልካች አዕምሮ ውስጥ ተቀምጦ የነበረውን 'አይዶል(idol) የሚለውን ቃል በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማስረሳት አስችሏል፡፡ ይሄ ዘዴም ጥበብ በተገቢው መንገድ ሲቀርብ ለውጥ ማምጣት እንደሚችል እንደማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡እንደ ቀደመው ልማድ ድንገት ከመሬት ተነስቶ በሬዲዮ እና በቴሌቪዥን ስማችንን ቀይረናል ተብሎ ቢነገር ኖሮ ይህን ያህል ተቀባይነት ማግኘት በከበደ ነበር፡፡ ለዚህ የበሰለ አካሄድና የአስተሳስብ ለውጣችሁ አጨብጭቤያለሁ፡፡<br />
<br />
በተጨማሪ ባላገሩ ምርጥን ምርጥ የሚያሰኘው ዋነኛው ነጥብ ኢትዮጵያዊነትን ለማንፀባረቅ መሞከሩ ነው፡፡ እያንዳንዱ የሚጠቀሟቸውን ነገሮች የሚገልፁት በኢትዮጵያውያን መገለጫዎች ነበሩ፡፡ ዋሽንቱ፣ አካፋው፣ አልባሳቱ እንዲሁም ለውድድሩ ድጋፍ ሠጪ ለሆኑት አካላት የሚሰሩ የንግድ ማስታወቂያዎች በሙሉ ኢትዮጵያዊነት የሚናገሩ ፣ አኗኗራችን የሚያሳዩ፣ አለባበሳችንን ፣ ጀግንነታችንን የሚያጎሉ ሲሆኑ ከሁሉ በላይ እያንዳንዱ ስራ ከውድድሩ ፅንሰ-ሃሳብ ጋር አብሮ የሚሄድ፣ የማዝናናት አቅማቸው ከፍ ያለ እንዲሆኑ ተደርገው የተሰሩ ናቸው፡፡ እንደዚህ አይነት ዘዴዎች ደግሞ የማንነት ቀውስ አባዜ ለጠለፋት ፣ ህዝቦቿም ኢትዮጵያዊነት መኩሪያ ሳይሆን መታፈሪያ እየሆነባት ላለች ሀገር ጠቀሜታው ትልቅ ነው፡፡ ሀገርን፣ ባህል ስርዓትን፣ መከባበር መዋደድን፣ ቅርስና ታሪክን እንዲሁም ሃይማኖታዊ አንድምታዎቻችንን ጠብቆ ይዞ ለመሄድ ይህን መሰል አቀራረቦች በጣም ያስፈልጋሉ፡፡<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiQ7TkA4TB6l4ah06gG05FfWFV4EEAbjIIzob5aywkyRnW9IsOF6oiIGvDMOgKs6G0V1DG-v5dQZ-Aekkdy6SfifcBsq4Q-0ggXdtsbX2tzJriN2JR6XzmgN5v81J0WcBuYDsyVYA1Ykuk/s1600/11062395_170752059927265_1839803502234429628_n.png.jpg%253Fefg%253DeyJpIjoiYiJ9%2526oh%253D58fcbe5d205caa3a1955b26a51fa8569%2526oe%253D56922CDE.jpg" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img border="0" height="200" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiQ7TkA4TB6l4ah06gG05FfWFV4EEAbjIIzob5aywkyRnW9IsOF6oiIGvDMOgKs6G0V1DG-v5dQZ-Aekkdy6SfifcBsq4Q-0ggXdtsbX2tzJriN2JR6XzmgN5v81J0WcBuYDsyVYA1Ykuk/s200/11062395_170752059927265_1839803502234429628_n.png.jpg%253Fefg%253DeyJpIjoiYiJ9%2526oh%253D58fcbe5d205caa3a1955b26a51fa8569%2526oe%253D56922CDE.jpg" width="200" /></a></div>
<br />
ሌላው ደሞዛቸውን ባላውቅም የውድድሩ አዘጋጆችም የዚህ ዓላማደጋፊዎች መሆናቸው አንዱ መልካም ጎኑ ነው፡፡ በተለይ ዋና አዘጋጁ አብረሃም ወልዴ ለኢትዮጵያዊነቱ የሚሰጠው ቦታና ክብር ያለው ቀናይነት በጣም ደስ ይላል፡፡ ይህን አስተሳሰቡንና ስሜቱን ተጋርተው ለዚህ ዓላማ ይጠቅሙኛል ይበጁኛል ብሎ የመረጣቸውን ባለሙያዎች ብዙ እንደደከመባቸው እና ፕሮግራሙ የተሸከመውን ትልቅ ሀገራዊ ተልዕኮ ተረድተው የተረዱትንም ወደራሳቸው አምጥተው ወደ ተግባር እንዲቀይሩ የማድረጉ ነገር ከባድ እንደሆነበት አስባለሁ፡፡ ያም ቢሆን ግን በተወሰነ መልኩ የተሳካለትም ይመስለኛል፡፡<br />
ወደፊትም የአብርሃም ችግርና ፈተና ብዬ የማስበው ሙያቸውን አክብረው በሙያቸው ብቁ የሆኑትን ባለሙያዎች ማግኘቱ ላይ ነው፡፡ምክንያቱም ሀገራችን ውስጥ ያሉ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ከስራቸው ውጪ ተናግሮ የማሳመን እንዲሁም ራሳቸውን በማንበብ ከጊዜው ጋር የለማራመድ የሚጥሩ ናቸው ብዬ አላምንም፡፡ ለምሳሌ በውድድሩ ላይ የሚገኙት የዳንስም ሆነ የድምፅም ዳኞች ከቀደመ ስብዕናቸው እና ከቀደመ ስራቸው በተለየ በዚህ የማወዳደር እና የመዳኘት ስራቸው ጠንካራ ፈተና የገጠማቸው መሆኑን ማወቅ አይከብድም፡፡ እነሱ ቀለል ለማድረግ ቢፈልጉ እንኳን ዋና አዘጋጁ እንዲህ በቀላሉ የሚተዋቸው አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም ውድድሩን እና የውድድሩን አቀራረብ ከዚህ ቀደም ከታዩት እጅጉን የተሻለና የበለጠ ለማድረግ እንደሚፈልግ በግልፅ ስለሚታይ፡፡ ይህን ለማረጋገጥ ካስፈለገ ስንት ዳኞች በውድድሩ እንደተለዋወጡ ማሰብ ቀላል ነው፡፡ ተቀይረው የመጡትስ ምን ዓይነት ናቸው ብለን ስናይ የአብርሃምን ድካም እንረዳለን፡፡ እነ ጋሽ አበራ ሞላ ፣ እነ ዳግማዊ አሊ የመሳሰሉት ጎበዝ ዳኞች እንደነበሩና ኢትዮጵያዊነትን ቅድሚያ የሚሰጡ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ ከዛስ? የተቀየሩት ዳኞች የቀድሞዎቹን ይመጥናሉ? እዚህ ላይ የተወሰነ ክፍተት እንዳለው ይሰማኛል፡፡ አሁን ካሉት ዳኞችም ባላገሩ ምርጥን የማይመጥኑ እንዳሉበት ይሰማኛል፡፡ በተለይ በዳንስና በውዝዋዜ ላይ፡፡ ትንሽ መውደድ ክብሩ ሲጨመር ተሽሎኛል፡፡ እነ እንዬም ወንበሩ ላይ ሲቀመጡ ምን ያህል የተወዳዳሩዎቹ ደስታ እንደጨመረ ማስተዋል ችያለሁ፤ የውድድሩም ግርማ ሞገስ ከፍ አድርጎታል፡፡ ተጋባዥ የድምፅ ዳኞቹም በተለይ ፒያኒስቱ ይፍራሸዋ ምን ያህል የበሰሉ እንደነበረ በደንብ ታይቷል፡፡ ቢቻል እነዚሁኑ ባለሙያዎች ይዞ መቀጠል የሚቻልበት መንገድ ቢመቻች ጥሩ ነው፡፡ እዚህ ላይ ብዙ ችግር ሊኖር ይችላል፤ የሙያተኛ እጥረትና ተባብሮ የመስራት ችግርም አብሮ እንዳለ ነው፡፡በሙያው ብቁ የሆኑትም እራሳቸውን ገለል አድርገው በሩቁ እንደሚኖሩም አውቃለሁ፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ ሀገሩቷ ያፈራቻቸውን ባለሙያዎችን ለመጠቀም እየተሞከረ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ይህን ሃሳቤን የሚያጠናክርልኝ አብርሃም ትልልቅ የሚባሉ ባለሙያዎችን ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ይጋብዝ ነበር፡፡ በየክልሉ ያሉትን ተወዳዳሪዎች በራሳቸው ሀገር ተወላጆች እንዲዳኙ ለማድረግ ሲጥር ተመልክቻለሁ፡፡ ይህ ደግሞ ይበልጥ ለተወዳዳሪዎቹም ሆነ ለተመልካቾች አሰልቺ እንዳይሆን እንዳደረገው ይሰማኛል፡<br />
፡ የዳኞቹ የዕድሜ ስብጥርም ሌላው የውድድሩ ማጣፈጫ ነበር፡፡<br />
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiFiVSiLLyDQK9VhzX3LT0dVHGWrJ0Bcmhyphenhyphenkbc-abDgYcmDp_GnEYhLeCLujaAkBi7D8SrEcg4drGRiLVUpCNy4k_Ge8RhTRYiU9VBINeEsI0w3udPROgQMaY51CsX2I2qHYuo7XnAt1ME/s1600/12047169_173173609685110_1946821839755034340_n.jpg%253Fefg%253DeyJpIjoiYiJ9%2526oh%253Dabe844a67e1568092f0057b4b785fbec%2526oe%253D56AA2F76.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="216" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEiFiVSiLLyDQK9VhzX3LT0dVHGWrJ0Bcmhyphenhyphenkbc-abDgYcmDp_GnEYhLeCLujaAkBi7D8SrEcg4drGRiLVUpCNy4k_Ge8RhTRYiU9VBINeEsI0w3udPROgQMaY51CsX2I2qHYuo7XnAt1ME/s320/12047169_173173609685110_1946821839755034340_n.jpg%253Fefg%253DeyJpIjoiYiJ9%2526oh%253Dabe844a67e1568092f0057b4b785fbec%2526oe%253D56AA2F76.jpg" width="320" /></a></div>
<br />
በዚህ መልክ የቀጠለው ውድድር በመጨረሻው ቀን ላይ ምን ተፈጠረ . . . ?<br />
<br />
<div style="text-align: center;">
<span style="color: blue; font-size: large;">የውድድሩ ፍፃሜ</span></div>
<br />
የውድድሩ ፍፃሜ ስገመግመው መልካም የሚባሉ ነገሮች የበዙትን ያህል የዛኑ ያህል ደግሞ ስህተቶች የነበሩት ነበር፡፡ የአብርሃም ልፋት ብዙ ከመሆኑ የተነሳ እሱ እራሱ በፍፃሜው ዝግጅት እንዳልተደሰተ ያስታውቅ ነበር፡፡ ይህ ክፍተትም የተፈጠረው አብርሃም ህክምና ላይ በነበረ ሰዓት መሆኑ ይበልጥ ያበሳጫል፡፡ የልፋቱም ውጤት ሙሉ እንዳይሆን አድርጎበታል፡፡ እስቲ እኔ የታዘብኩትን ችግሮች ልዘርዝር፡-<br />
<br />
<span style="color: red;">1ኛ. የቅንጅትችግር</span><br />
<br />
መድረክ መሪዋ ትዕግስት እራሷን ፈፅሞ ማረጋጋት ተስኗት ነበር፡፡ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር የተፈራረመቸው እሷ ነበር የምትመስለው፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን ማመን ከባድ ሊሆን ቢችልም የአብርሃም በተደጋጋሚ እሷን ሊያቋርጣት መሞከሩ ግን ማነው የፕሮግራሙ መሪ አዛዥ ያስብላል፡፡ እሷ ጊዜ የለም ትላለች አብርሃም ደግሞ የአመታት ድካሙ ውጤቶች የሆኑትን ልጆች መድረክ ላይ መውጣት አለባቸው ይል ነበር፡፡ በግሌ በአብርሃም ሃሳብ እስማማሉ፡፡ ምክንያቱም ለውድድሩም ድምቀት፣ ለተወዳዳሪዎቹም ክብር፣ ለውድድሩም ፍፃሜ ማማር የሚበጀው ሁሉንም መድረክ ላይ ማየት ነበር፡፡ ይሄ ደግሞ በየትኛውም ዓለም የሚደረግ የስነስርዓት አካሄድ ነው፡፡ እዚህ ላይ ከቴሌቪዥን ጣቢያው ጋር የተደረገው የሰዓት ርዝማኔ ስምምነት ይጣስ እያልኩኝ ባይሆንም ቅድሚያ መሰጠት ያለበት ለተወዳዳሪዎቹ ልፋትና ድካም እንዲሁም ክብር ነው፡፡<br />
ሰዓት የለንም እያለች አስሬ ከመረበሽ ቀደም ተብሎ ስራ ቢሰራ በቂ ሰዓት እንዲኖር ማድረግ ይቻል ነበር፡፡ ግን የቅንጅት ስራ አልነበረም፡፡ ጊዜ አጠቃቀም ላይ ደካማ ነበሩ፡፡ ዳኞች ማውራት አልቻሉም ነበር፡፡ ጭራሽ ሴቷ ተወዳዳሪ እየዘፈነች በመሀል ይቅርታ አቁሚ ተብላ ከስሜትም ከነበረችበት ተመስጥዖ ተረብሻ እንደገና እንድትጀምር ተደርጋለች፡፡ይሄ አሳፋሪ ድርጊት ነበር፡፡ መድረክ መሪዋ ሬድዮ ላይ የምታወያይ መስሏትይሆን ? ድፍረቷና ችኩልነቷ የብዙዎችን ቆሽት ያሳረረ እና የውድድሩን ክብር የማይመጥን ነበር፡፡ ሌላው ደግሞ ዓመቱን ሙሉ አስተያየታቸው ሲሰማ ምስላቸው ተደጋግሞ ሲታይ የነበሩ ዳኞች የድካማቸው ውጤት እንዴት እያጣጣሙ እንዳለ ማየት አልቻልም፡፡ ምን እየሰሩ እንዳሉ፣ አስተያየታቸውን መስማት፣ ስሜታቸውን መመልከት አልተቻለም፡፡ እንዲሁም የተወዳዳሪዎቹን ደስታና ሀዘን መመልከት አልቻልንም፡፡ ይልቅ ሰዓት ቁጠባ ተብሎ ከመድረኩ ቶሎ እንዲወርዱ ነበር ሲነገራቸው የነበረው፡፡ ውድድሩ የማን ነበር? የልጆቹ አልነበረምን ? ሊገባኝ አልቻለም፡፡<br />
ይህን ሁሉ የሚያስብለኝ በቀደመው በውድድር ጊዜያች አብርሃም ለተወዳዳሪዎቹ እና ለውድድሩ ትልቅ አክብሮት ነበረው፡፡ በተጨማሪም ይህ ነው የሚባል የጎላ ስህተት ላለመስራት ሲጥር ስለነበርነው፡፡ የውድድሩም ደረጃ ከፍ እንዳለ ለመፈፀም የነበረውን ጥንቃቄ ስለማስብ ነው፡፡ ግን በመድረክ መሪዋ ረባሽነት እና በቅንጅት ማነስ እንደታሰበው ሳይሆን ቀረ፡፡<br />
<br />
<span style="color: red;"> 2ኛ. የመብራት እና የቀረፃ ችግር</span><br />
<br />
የተወዳዳሪዎቹን ስም ባላውቅም በዘመናዊ የዳንስ ውድድር ላይ ለነበሩት ልጆች በጣም የሚያናድድ ቀን እንደነበረ አስባለሁ፡፡ ሙሉ ስራቸው ከመብራት መጥፋትና ጭለማ መሆን ጋር የነበረ ቢሆንም የመብራት መጥፋትና መብራቱ እንደፈለጉት አለመሆን ድካማቸውን ዋጋ እንዳይኖረው አድርጎታል፡፡ አብርሃምም ይህን ተረድቶ ይመስለኛል ይቅርታ ሊጠይቅ የሞከረው፡፡ የሱ አለመኖር ልጆቹን ዋጋ አስከፍሏቸዋል፡፡ ቅሬታቸውንም እንደሚክስላቸው አስባለሁ፡፡ የነበራቸውን ተነሳሽነትና ፍላጎት ማሳየት የሚፈልጉትን ማሳየት ባለመቻላቸው እንደሚከፉ ግልፅ ነው፡፡ ትልቁ ነገር የአብርሃም ለተወዳዳሪዎቹ የሚሰጠው ክብር እንዲሁም ተወዳዳሪዎቹን የያዘበት መንገድ ይቅር ያስብለው ይሆናል፡፡ ሌላው ቀረፃው ከዚህ ቀደም በተለይ በብሔራዊ ቲያትር የነበረውን ዓይነት መሆን አልቻለም፡፡ ከቀድሞዎቹ ቀረፃዎች ጋር ሲነፃፀር ደካማ ነበር፡፡ ይሄ ይሄ ብል አንባቢን ግራ ማጋባት ሊሆን ስለሚችል ልዝለለው፡፡ የካሜራ እና የዳይሬክቲንግ ባለሙያዎች ግን ይህን ሃሳቤን የምትጋሩኝ ይመስለኛል፡፡<br />
<br />
<span style="color: red;">3ኛ. የድምፅ አሠጣጥ</span><br />
<br />
አብርሃም በጣም ተሸወደ የምለው በዚህ ብቻ ነው፡፡ 60% የህዝብ ድምፅ 40% የዳኞች ብሎ መጀመሪያ በመናገሩ ተወዳዳሪዎች ላይ ተፅዕኖ ነበረው፡፡ እዚህ ላይ አብርሃምን የምረዳበት ነጥብ አለ፣ በህዝብ የተመረጠ ተወዳዳሪ መፍጠር ነበር ፍላጎቱ፡፡ ይህ ደግሞ ከአንድ ኃላፊነት ከሚሰማው ህዝብን አክባሪ ከሆነ የጥበብ ሰው የሚጠበቅ ነው፡፡ነገር ግን አብሮ ተያይዞ የሚመጣው ችግር የተጠና አልመሰለኝም፡፡ በተጨማሪ የህዝብ ምርጫ ተብሎ ውጤቱ በቴሌቪዥንም ይታይ ስለነበር ለተወዳዳሪዎችና ለደጋፊዎቻቸው ተስፋ አስቆራጭ ነበር፡፡ በተለይ የአሸናፊው የዳዊት ድምፅ ከሌሎቹ ተወዳዳሪዎች ጋር የሰማይና የምድር ያህል ልዩነት ነበረው፡፡ ይሄ ደግሞ የተወዳዳሪዎቹን ሞራል ያደከመው ይመስለኛል፡፡ ይህን በመገንዘብ መሰለኝ ከህዝብ ድምፅ ይልቅ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የዳኞችድምፅ መሆኑን ውድድሩ ከተጀመረ በኋላ ለማስተካከል የተሞከረው፡፡ ውሳኔው ጥሩ የነበረ ቢሆንም በጣም ዘግይቶ ነበር፡፡<br />
ቅሬታዬ ግን መጀመሪያም ህዝብ መምረጥ አለበት ተብሎ ሲወሰን ለምን ጥንቃቄ ማድረግ አልተቻለም ነው፡፡ በግሌ የህዝቡ ድምፅ 60% ሳይሆን 10% ወይም 15% ብቻ ቢሆን በቂ ይሆናል ብዬ አስባለሁ ፡፡ ምክንያቱም አንደኛ የተወዳዳሪዎቹ የምረጡኝ ዘመቻ አለመመጣጠን ነበረበት፡፡ ለምሳሌ ዓይነስውሩ ባልከው እና አሸናፊው ዳዊት ህዝብን ምረጡኝ ብሎ ለመቀሰቀስ እኩል አቅም ያላቸው አይመስለኝም፡፡ ሴቶቹም ቢሆኑ ከወንዶቹ እኩል ይሆናሉ ብሎ መገመት የዋህነት ነው፡፡ ምክንያቱም ይሄ ኢትዮጵያ እንጂ አሜሪካ ወይ አውሮፓ ስላልሆነ፡፡ በተጨማሪም የህዝቡ ንቃተ-ህሊና በራሱ ገና የሚቀረው ነው፡፡ ይሄ ደግሞ ህዝብን መናቅም ሊሆን አይችልም፤ እውነታን መጋፈጥ ስላለብን ነው፡፡<br />
<br />
******* *******<br />
<br />
በመጨረሻ የባላገሩ ምርጥ እስከዛሬ በኢትዮጵያ ከተካሄዱት ውድድሮች በጣም የተሻለና የብዙ ባለሙያዎች ድካምና ልፋት የነበረበት ነው፡፡ በአንድ ወቅት የኢትዮጵያ አይዶል በነበረበት ጊዜ የውድድሩ ሀሳብ አመንጪ እኔ ነበርኩ ዓይነት ክርክሮች በአብርሃም እና በጀማል መሀከል እንደነበረ አስታውሳለሁ፡፡ ይህም አሁን ላይ ለአብርሃም ጥንካሬ እና የተሻለ ነገር የመስራት አቅም እንደሰጠው እገምታለሁ፡፡ በቀጣይ ዓመታትም ከቀደመው ስህተቶች በመማር የተሻለ እና ተመራጭ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ያስፈልጋል፡፡ በሙያቸው አንቱ የተባሉን በማካተት ጥሩ ጥሩ ባላገሮችን ማፍራት ይቻላል፡፡ በተረፈ ለዋና አዘጋጁ አብርሃም ወልዴ ያለኝን እክብሮት መግለፅ እፈልጋለሁ፡፡ ጤንነቱ ወደቀድሞ ተመልሶ ያሰበውን ያሳካ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው፡፡<br />
<br />
<span style="font-size: large;">ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር፡፡</span><br />
<br />
<br />
<br />
<br />
<br />
<br />
<br />
<div>
<br /></div>
</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-33040794900588186532015-09-20T23:23:00.003+03:002015-09-22T17:38:57.522+03:00እነሆ ባቡሩ...<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg4Yj4G0a_ufiGqOSYpkccaly-fO4YBnKdZBdEb5DbLlkSu_cNbNRaGdLe9qN73I8ILN5GuEPSEmUw7OcylWdIwL7TKcLzFXeQe00RkpYRy62IKw2X_69Z_2PyxBZBVs7B-wdktuER-cOc/s1600/Ethiopian+train+%25E1%2589%25A3%25E1%2589%25A1%25E1%2588%25AD++%25E1%2589%25A0+%25E1%258A%25A2%25E1%2589%25B5%25E1%258B%25AE%25E1%258C%25B5%25E1%258B%25AB+1+bisrat+gebre+views+.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="178" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg4Yj4G0a_ufiGqOSYpkccaly-fO4YBnKdZBdEb5DbLlkSu_cNbNRaGdLe9qN73I8ILN5GuEPSEmUw7OcylWdIwL7TKcLzFXeQe00RkpYRy62IKw2X_69Z_2PyxBZBVs7B-wdktuER-cOc/s320/Ethiopian+train+%25E1%2589%25A3%25E1%2589%25A1%25E1%2588%25AD++%25E1%2589%25A0+%25E1%258A%25A2%25E1%2589%25B5%25E1%258B%25AE%25E1%258C%25B5%25E1%258B%25AB+1+bisrat+gebre+views+.jpg" width="320" /></a></div>
<br />
ዛሬ ነው መስከረም 8 , 2008 ዓ.ም<br />
<br />
ንጋት ላይ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን (ፒያሳ) አካባቢ ነበርኩ፡፡ በእሳት አደጋ መ/ቤት አካባቢ ባለው የቤተክርስቲያኑ በር የተወሰ ግርግር ነበርና ምናልባት ሰንበት ስለሆነ የሚያስቀድሱ ሰዎች ይሆኑ ብዬ አሰብኩ፡፡ ግን ፖሊሶች (ፌደራሎች) በዛ ብለው ሳይ ምን ተፈጥሮ ነው ብዬ አንዲት ነጠላ የለበሱ እናትን ጠየኳቸው ' ባቡሩ. . . መሠለኝ" አሉኝ<br />
<br />
" ባቡር ስራ ይጀምራል" የሚለው ትዝ አለኝና ወደ ጉዳዬ አዘገምኩ፡፡<br />
<br />
ከረፋዱ 4 ሰዓት አካባቢ ጉዳዬን ፈፅሜ ስመለስ በግምት ከሁለት መቶ እስከ ሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ሰልፍ
ይዘዋል፡፡ ተጠማዞ ተጠማዞ እረጅም ሰልፍ ሆኗል፡፡ የባቡሩን ነገር እረስቼው ስለነበር ምን ተፈጠረ ብዬ ሁኔታውን
ለማጣራት ቆምኩኝ፡፡ ባቡር ሊሳፈሩ እንደሆነ<br /> አንዱ ሠልፈኛ ነገረኝ፡፡ ይሄ ሁሉ ህዝብ በአንድ ግዜ ለባቡሩ እንዴት<br />
ሊሆን ይችላል አልኩ ለራሴ፡፡ ዝንጥ ያሉ ወጣቶች ፣ እናቶች አባቶች ጎረምሶች ፣ ቀበሌ ፊት ፣ ክፍለ ከተማ ፊት
ተብሎ በልምድ የሚነገሩ ፊት ያላቸው ሰዎች . . . ብቻ ብዙ ዓይነት ሰዎች ተሠልፈዋል፡፡ ሠልፉን ከፊት የሚመሩት
ትኬት መቁረጫ ይመስለኛል አንድ ትልቅ ኮንቴነርን ከበዉታል፡፡<br />
<a name='more'></a><br />
ገርሞኝ ትንሽ እንዳለፍኩ ካሜራዎች ተደርድረው ቀረፃ ላይ ናቸው ፡፡ 'ኢንተርቪው' የሚደረጉ ሰዎች ካሜራው አካባቢ ቆመዋል፡፡ ኢቲቪ ጀግናው ስራውን በአግባቡ እየሠራ ነው አልኩ ለራሴ ፡፡<br />
<br />የባቡር ስራው መጀመሩ መልካም ቢሆንም ሰውን የሚያክል ነገር<br /> አሰልፎ የፖለቲካ ማስፈፀሚያ ማድረግ ግን ተገቢ
ነው ብዬ አላምንም ፡፡ የሠልፉ ግርግር የውሸትም ይሁን የእውነት ለአዲስ አበባ ህዝብ አይጠቅመውም ፡፡ ምክንያቱም
ከጅማሬው ይህን ያህል ህዝብ ከተሠለፈ በቀጣይ ደግሞ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሰብ ቀላል ነው ፡፡ ታክሲዬ የኔ
ፍቅር ብሎ ከታክሲው ጋር ወዳጅነቱን መቀጠል ነው የሚጀምረው ፡፡ የትራንስፖርት ችግርን ይቀርፍልካል ተብሎ ሲሰበክ
ለኖረ ህዝብ ገና ከመጀመሪያው ይህን የመሰለ ረጅም ሰልፍ ከተመለከተ ባቡሩ ላይ የተመኘውን ተስፋ በመጀመሪያው ቀን
ይጥለዋል፡፡ ባቡሩ ስራ ጀመረ ተብሎ ብሎ ማክበር ባይከፋም የህዝብ ጋጋታ ማሠለፍ ግን ላሰራው አካል ትልቅ ፖለቲካዊ
ኪሳራ ነው፡፡<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEioZyVMFf-Avw2DB22YVyp0kE9AqfWY7vOWDBjSM0mTQWQUGGm1cW8pLPHH1HjaNgdl78fcQ0_6vHEn4__8BihtHxjFar2VVYP2Ik7bLMxDhZRPbpZa9uuR-F6vX7b0GXAI3ne38GaFbyA/s1600/Ethiopian+train+%25E1%2589%25A3%25E1%2589%25A1%25E1%2588%25AD++%25E1%2589%25A0+%25E1%258A%25A2%25E1%2589%25B5%25E1%258B%25AE%25E1%258C%25B5%25E1%258B%25AB+bisrat+gebre+views+1+.jpg" imageanchor="1" style="margin-left: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="139" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEioZyVMFf-Avw2DB22YVyp0kE9AqfWY7vOWDBjSM0mTQWQUGGm1cW8pLPHH1HjaNgdl78fcQ0_6vHEn4__8BihtHxjFar2VVYP2Ik7bLMxDhZRPbpZa9uuR-F6vX7b0GXAI3ne38GaFbyA/s320/Ethiopian+train+%25E1%2589%25A3%25E1%2589%25A1%25E1%2588%25AD++%25E1%2589%25A0+%25E1%258A%25A2%25E1%2589%25B5%25E1%258B%25AE%25E1%258C%25B5%25E1%258B%25AB+bisrat+gebre+views+1+.jpg" width="320" /></a></div>
<br />
አዲስ አበባ ህዝብ ካለበት ችግሮች አንዱና ዋነኛው የትራንስፖርት እጦት ነው፡፡ " ይኸው ተመልከት. . .
ሠልፉን . . . የባቡርን ስራ መ'ጀመር በጉጉት ሲጠብቅ የነበረ ህዝብ በደስታ ወጥቶ ተሠለፈ ፤ ከታክሲ ችግር
አይበልጥብንም ብሎ ገና በጠዋቱ ተሠለፈ " ብለን ብንደሰኩር ማንም አይሠማም፡፡ የአዲስ አበባ ህዝብ ችግርን
ከመላመዱ የተነሳ የማንንም እርዳታ ሳይሻ በራሱ የህይወት አመራርና መንገድ መኖር ከጀመረ ቆይቷል፡፡ <br /> መንገድ ትራንስፖርት የሚባለው መስሪያ ቤትም አይደለም የህዝቡን ችግር ሊፈታ. . . የሚያወጣውን ህግና ስርዓት ከህዝብ ጋር ተባብሮ መቆጣጠር ያልቻለ ሚኒስተር መ/ቤት ነው፡፡<br />
<br />
ይህን ሁሉ ችግር ችሎና ታግሶ ፣ ተጣልቶና ተስማምቶ የሚኖርን ህዝብ ይኸው ባቡርክ ስንለው በምን መልክ መሆን እንዳለበት ማሠብ ነበረብን ፡፡ አሁንም አለብን፡፡ ልንዋሸው ልናታልለው አይገባም ፡፡<br />
<br />
ለዛሬው በዚሁ አበቃሁ፡፡<br />
<br />
<br />
<span style="color: red;">ኢትዮጽያ ለዘለዓለም ትኑር!</span></div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com2tag:blogger.com,1999:blog-3788642389341462324.post-31271277037338179062015-08-19T22:23:00.002+03:002015-08-21T17:33:16.212+03:00ደብረ ታቦር<div dir="ltr" style="text-align: left;" trbidi="on">
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhdLmVtTZOmhH5jjSNBliGzhZBuj9svHCuULwSWIEE3U-zUgIaWzxFmSKCGzVq40Y5NbXhTvaO4kBFJ3RjjDVO5eqQ4rfPJES6Lokdmp7wW5NOyPXtjZQKSjfLjzMhCflnz8o_Uwd_nWbE/s1600/images.jpg" imageanchor="1" style="clear: left; float: left; margin-bottom: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="236" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEhdLmVtTZOmhH5jjSNBliGzhZBuj9svHCuULwSWIEE3U-zUgIaWzxFmSKCGzVq40Y5NbXhTvaO4kBFJ3RjjDVO5eqQ4rfPJES6Lokdmp7wW5NOyPXtjZQKSjfLjzMhCflnz8o_Uwd_nWbE/s320/images.jpg" width="320" /></a></div>
ደብር ማለት ተራራ ማለት ሲሆን ፤ ታቦር ደግሞ የተራራው ስም ነው፡፡ ቃሉ በአንድነት ሲነበብ ደብረ ታቦር ይሆናል፡፡ ይህም የታቦር ተራራ የሚል ትርጉም ይሠጠናል፡፡ ደብረ ታቦር ከገሊላ ባሕር በምዕራባዊ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ተራራ ሲሆን ከፍታው ከባሕር ወለል በላይ 572 ሜትር ይሆናል፡፡ ከተራራው አናት ላይ 100 ሜትር በ400 ሜትር ስፋት ያለው ደልዳላ መስክ ይገኛል፡፡ በቅዱስ ወንጌል እንደምናገኘው በዚህ ተራራ ጌታችን በዘመነ ሥጋዌው በሚያስተምርበት ወቅት ምስጢረ መንግስቱንና ብርሃነ መለኮቱን ገልጧል፡፡ በዚህ የተነሳ ይህ ተራራ በክርስትና ታሪክ ትልቅ ስፍራ አለው፡፡ በማቴ. 17፡ 1-13 ላይ የተፈጸመው ተዓምር እንዲህ ነበር፡፡<br />
ጌታችን አዕማድ ተብለው የሚጠሩ ሶስቱን ሐዋርያት ይዞ ወደ ተራራ ወጣ፤ በዚያም በፊታቸው ልብሱ እንደ በረዶ ነጭ ሆነ፡፡<br />
<a name='more'></a>መልኩም ተለወጠ፡፡ ፊቱ እንደ ፀሐይ አበራ፤ በዚህ ጊዜ ሙሴ እና ኤልያስ ተገልጠው ማነጋገር ጀመሩ፡፡ ሙሴ በኦሪት ፊትህን አሳየኝ ብሎ የለመነውን ከሙታን አስነስቶ ስለ ክብሩ የቀናውን ኤልያስንም ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ ክብሩን አሳይቷቸዋል፡፡ ሙሴ በህገ ጋብቻ ያለፈ ነብይ ነው፡፡ ኤልያስ ደግሞ በድንግልና እና በምነና ኖሮ ያረገ ነው፡፡ ሁለቱ መገለጣቸው ቤተክርስትያን በጋብቻ እንዲሁም በድንግልና (በምነና) የሚኖሩ አባቶች መኖሪያ እንደሆነች ለመግለፅ ነው፡፡ ከሶስቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ጴጥሮስ በሁለተኛይቱ መልዕክት 2ኛ ጴጥ. 1፡ 17-18 ‹‹ ከከገናናው ክብር በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና እኛም በቅዱስ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህን ድምፅ ከሰማይ ሰማን፡፡ ›› እንዳለ፤ በማቴ. 17፡4-5 ላይ ጌታ ሆይ በዚህ ለኛ መሆን መልካም ነው ብትወድስ በዚህ ሶስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንስራ አለ፡፡<br />
<br />
<div class="separator" style="clear: both; text-align: center;">
<a href="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjmHu6Qa1EmnunEIi4XFTyFJvOJvQ2x0Y5iKuFXMN4PUMF4tj0N6-LwHuokW6HiILeYiPRP10RzvH_m2u_IeTmVtQguA3tHyrM_7L9wdyqYbIm2omVxZMvJJfB9E1vlPj3Gok5w3ktwIws/s1600/DebreTabor_Icon.gif" imageanchor="1" style="clear: left; float: left; margin-bottom: 1em; margin-right: 1em;"><img border="0" height="320" src="https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEjmHu6Qa1EmnunEIi4XFTyFJvOJvQ2x0Y5iKuFXMN4PUMF4tj0N6-LwHuokW6HiILeYiPRP10RzvH_m2u_IeTmVtQguA3tHyrM_7L9wdyqYbIm2omVxZMvJJfB9E1vlPj3Gok5w3ktwIws/s320/DebreTabor_Icon.gif" width="240" /></a></div>
እዚህ ላይ ‹‹ ብትወድስ›› ያለው (ፈቃድ የጠየቀው) ከዚህ በፊት በቂሳርያ አይሁንብህ አይደረግብህ በማለቱ ተገስፆ ስለነበር ነው፡፡ ማቴ. 16-22፡፡<br />
በዚህ ግዜ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው ከደመናውም በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ ተሰማ፡፡ ይህ ድምፅ አብ ስለ ልጁ የመሰከረበት ነበር፡፡ ሐዋርያት ይህን ድምፅ ሰምተው የጌታችንን መለኮታዊ ክብር አይተው በፊታቸው ወደቁ፡፡ እጅግም ፈርተው ነበር፤ ጌታችን ዳሰሰና አነሳቸው ፤ ተነሱ አትፍሩ አላቸው፡፡ በዚህ መልኩ አምላክነቱን ገለጠላቸው፡፡ የሕያው እግዚአብሔር ልጁ መሆኑን ምስጢር ተረዱ፡፡ ስለዚህ ደብረ ታቦር ምስጢረ መንግስቱንና ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል በመሆኑ በቤተክርስቲያናችን ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ ስለሆነ ነሐሴ 13 ቀን በዓሉን ታከብራለች፡፡<br />
ደብረ ታቦር የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው ፡፡ ከምሳሌዎቹ በጥቂቱ ስናነሳ፡-<br />
<br />
<br />
<ol style="text-align: left;">
<li>ደብረ ታቦር ድል ለማድረግ የሚመች ተራራ ነው፡፡ አካባቢው ከፍ ያለና ከታች ያሉትን ሸለቆዎች ሁሉ ለመቆጣጠር የሚመች ስለሆነ ነገስታቱ ለጦርነት ይመርጡታል፤ በጦርነትም ታቦርን የያዘ ድል ያደርግ ነበር፡፡ ለምሳሌ ፡- ዲቦራና ባርቅ ሲሣራን ድል ያደረጉት ይህንን ተራራ በመያዛቸው ነውሀ፤ መሳ. 4፡7 ታሪኩን ስናነብ እንደምናገኘው ከጦርነቱ በፊት ነቢይቱ ዲቦራ ባርቅን ጠርታ ይህንኑ ነግራዋለች ፤በዚህ አባባሏ ባርቅ ድል ለማድረግ ወደ ታቦር ተራራ መውጣት እንደነበረበት እንረዳለን፡፡ በመሆኑም ባርቅ ይህን የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ሰምቶ ወደ ታቦር ወጣ፡፡ ከዚያም ኃይልን አግኝቶ በመውረድ ሲሣራን ድል አደረገ፡፡ እንደዚህ ቤተክርስቲያን የደብረ ታቦር ምሳሌ በመሆኗ ድል ማድረጊያ ቦታ ናት፡፡ ወደ እርሷ የመጣ ኃይል አግኝቶ ጠላቱን ያሸንፋል፡፡ በእግዚአብሔር ኃይል በፆምና በፀሎት መንፈሳዊ ተግባራትንም በማድረግ ሰይጣንን ድል ያደርጋል፡፡</li>
<li>ደብረ ታቦር 572 ሜትር ከፍታ ያለው ሲሆን ፤ ከዚህ የተነሳ ወደ ላይ ሲወጡት አስቸጋሪ ዳገት ሆኖ ከወጡት በኋላ አናቱ ላይ ሲደረስ መስክ አለ፡፡ በዚህ የተነሳ ወደዚህ ተራራ የሚወጣ ሰው ሁሉ ከብዙ ድካም በኋላ ደልዳላውን ስፍራ (መስክ) ሲመለከት ደስ ይሰኛል፡፡ ድካሙንም ይረሳል፡፡ ቤተክርስቲያንም የደብረ ታቦር ታራረ ምሳሌ በመሆኗ ለጊዜው ሲቀርቧት ዳገት ትሆናለች፡፡ ፁሙ ፀልዩ ስገዱ መፅውቱ ስለምትል ታስፈራለች ፤ ከቀረቧት በኋላ ግን በውስጧ መኖር ሲጀምሩ ሰላም ትሰጣለች ፤ ፍፃሜዋ ደስ የሚያሰኝ እና ሰላማዊ ስለሆነች ታሳርፋለች፡፡ ጌታችን በወንጌሉ፡- ዩሐ. 14-27 ሰላሜን እተውላችኋለሁ፡፡ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ እኔየምሰጣችሁ ሰላም ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም የሚለን ለዚህ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ ደብረ ታቦር የቤተክርስቲያን ምሳሌ ናት፡፡ ይህን ተረድተን ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ መሆን ለኛ መልካም ነው እንዳለ እኛም ይህን ቃል እንድንፈፅም ከታቦር ቤተክርስቲያን ላንርቅ ቃል እንግባ፡፡</li>
</ol>
<br />
<br />
በታላቁ ገዳም በደብረ ሊባኖስ የደብረ ታቦር በዓል በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ በሰዓታቱ ፣ በማዕሌቱ ፣ በቅዳሴው ፣ በወንጌል አገልግሎት እንዲሁም የገዳሙ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ይዘክሩታል፤ የሚማሩት ትምህርት እንዲገለፅላቸው ፈጣሪያቸውን ይማፀኑበታል፡፡<br />
<br />
የደብረ ታቦር ምስጢር በእኛም ሕይወትና በልቦናችን ብርሃኑን እንዲያበራልን ወደቤተክርሰቲያን መቅረብ ይገባናል፡፡ ለዚህም እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን ፡፡ አሜን!!!<br />
<br />
<br />
<br />
<br />
<div style="text-align: right;">
<span style="color: red; font-size: x-small;">(ምንጭ፡- ፊልጶስ በሐምሌ </span></div>
<div style="text-align: right;">
<span style="color: red; font-size: x-small;">በመምህር አባ ወ/ገብርኤል ገ/ኢየሱስ እና ዲያቆን አባ ገብረ ጻድቅ ነገ )</span></div>
<br />
<br />
<br />
</div>
Bisrat Gebrehttp://www.blogger.com/profile/03566366269921318395noreply@blogger.com1