ሠላም ጤና ይስጥልኝ ክቡራን አንባቢያን ፤ ከዚህ መካነ-ድር (ድረ ገፅ) ላይ የምትወስዱትን ማንኛውንም ፅሑፍም ይሁን ምስሎች ለአዘጋጆቹ እና ለፀሐፊዎቹ ክብር ሲባል በምትጠቀሙበት ቦታ ሁሉ ምንጩን ትጠቅሱልን ዘንድ በትህትና እናሳስባለን ፡፡

Saturday, March 17, 2012

የታክሲ ውስጥ ጥቅሶች



‹ ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ አስተያየት፣ቅሬታ፣ትዝብት ወይም መሻሻል አለበት የምትሉት ነገር ካለ አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል ››
     ድሮ ልጅ በነበርን ጊዜ የትምህርት መፅሐፍትን ማንበብ ጎበዝ ስለሚያስብለን ማንበብ አሁንም ማንበብ ነበር ስራችን ፡፡ የህፃንነት አህምሮ እንደጉልምሳ ብዙም ስለማያስቸግር የተሰጠውንና የገባውን ነው የሚቀበለው፡፡ በወቅቱ ከትምህርት መፃህፍት ውጪ ማንበብ ጊዜን አልባሌ ቦታ እንደማዋል እና ከዓላማ መሳቻ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ ከጥቂቶች በስተቀር በአብዛኛል ተማሪ አትኩሮቱ ደብተሩና ተያያዥነት ያላቸው መፅሐፍት ላይ ነበር፡፡ ምናልባትም ወላጆች ያሳደሩት ተፅዕኖ ሊሆን ይችላል፡፡ ታዲያ ይህን አልፎ ሁሉን አቀፍ ዕውቀት ያለው ተማሪ ማግኘት ብርቅ የነበረ ሲሆን ከተገኘም ጓደኛ ለማድረግ ተመራጭና ቅድሚያ ይሰጠው ነበር፤ እንደጎበዝ ይቆጠራል፡፡ ‹‹ እሱ ወይም እሷ ያላነበበው/ያላነበበችው መፃህፍት፤ ያላነበበው/ያላነበበችው ልቦለድ የለም ›› ይባላል፡፡
አንባቢ ነው የተባለውም ተማሪ መለያው ምልክቱ ደብተሩ በአባባሎችና ጥቅሶች ያሸበረቀና የደመቀ መሆኑ ነበር፡፡ የግሪኩ ፈላስፋ የተናገረው፣ የአረቦች አባባል፣የቻይናዎች አባባል፣ የኢትዮጵያውን ብሂል ወዘተ. . . ወዘተ . . . እየተባለ የተገኘው ይፃፋል፡፡ ምንጭ ይጠቀሳል፡፡ በሆነ አጋጣሚ ደብተሩን ያየ ወይም ያገኘ የተፃፈውን ፅሑፍ እና አባባል ኮርጆ ለራሱ ያደርገዋል፡፡ ታዲያ ማንም ተማሪ ጋር የሌለ ጥቅስና አባባል የሚፅፍ የሚናገር ‹‹ እሱ እኮ! ፤ እሷ እኮ !›› ይባልላቸዋል፡፡

ሌላው በትምህርት ቤት ህይወት ውስጥ የመለያያ ወቅት የሚባሉት ማለትም ተማሪዎች የሚለያዩበት 8ኛ፣10ኛ ወይም 12ኛ ክፍል ሊሆን ይችላል የሚዘጋጅ በተለምዶ ‹‹ ማስታወሻ ደብተር (Autograph) ›› ተብሎ የሚጠራ በዛ ያሉ ጥያቄዎችና መጠይቆች ያሉበት ለየት ያለ ማስታወሻ ይዘጋጅ ነበር፡፡ ማስታወሻ ደብተሩ ላይ ጽጌሬዳ አበባ መሳል፣ግጥሞች መፃፍ የተለያዩ አስገራሚና አስቂኝ የሚባሉ ፅሑፎችን ማውጣት ዋና ስራ ነበር፡፡ ሁሉም አለኝ የሚለውን ይፅፋል፤ ያነበበውን ያካፍላል፤እራሱን ከሌሎች ጋር ያወዳድራል እንዲሁም እራሱን ሊያሳይ ይጥራል፡፡
ትንሽ ቆይቶ በአካልም በአስተሳሰብም እያደግን ስንመጣ ያ ሁሉ ነገራችብ ላይ መቀዛቀዝ ይታያል፡፡ ማንበብ ባይተው እንኳን  ለጥቅሶችና ለአባባሎች ያለን አትኩሮት ይቀንሳል፤ተፅዕኗቸውም  ይወርዳል፡፡ የዛሬን አያድርገውና በአንድ ወቅት በየመኖሪያ ቤቱ ግድግዳ ላይ በጥሩ የእጅ ፅሑፍ የተፃፉ አባባሎችን፣ ግጥሞችን ማየት የተለመደ ነበር፡፡ ብዙዎቹ አስተማሪና መካሪ ለሠዎች ቀና እንድንሆን፣ ወንጌልን የሚሰብኩና እግዚአብሔርን የሚማፀኑ ጥቅሶች ነበሩ፡፡ አንዳንዴም አሽሙሮችም አይጠፉበትም፡፡ በወቅቱ እንዲህ ዓይነት ነገሮችን ማግኘት የሚቻለው በ‹‹ጠላ›› ወይም ‹‹አረቄ›› እንዲሁም ጠጅ ቤቶች አካባቢ ነበር፡፡ ምናልባት የሰከረን ለመምከር፣ ለማስተማር ወይም ብሶቱን ከፍ ለማድረግ ይሁን አይሁን አላውቅም፡፡ የዋህ እና ደስ የሚል ጊዜ ነበር፡፡ታዲያ አሁንስ?
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ በታክሲዎች ውስጥና ውጪ የምመለከታቸው ነገሮች የድሮ እና ያለፉትን ጊዜያቶችን ያስታውሳሉ፡፡ በተለይ በአሁኑ ግዜ በያንዳንዱ ታክሲ ውስጥ ጥቅስና አባባሎች ማየት እየተለመደ ከመምጣቱም በላይ እንደአንድ የመግባቢያ መንገድ መቆጠርም ጀምሯል፡፡ እንደያኔው ባይበዛም አስተማሪና ምክር አዘል ነገር በጥቂቱም ቢሆን አላቸው፡፡ ነገር ግን ብዙዎቹ የማሳቅ ይዘት ያላቸውና በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለአንድ ለሚመለከተው አካል መልዕክትን  እንደ ማስተላለፊያ ዘዴ  ይጠቀሙበታል፡፡ እነዚህ ጥቅሶች ፖለቲካዊ፣ ሀይማኖታዊ እንዲሁም አሽሙራዊ ንግግሮች ከፍ ሲልም ስድቦች ያካትታሉ፡፡

አንድ ግለሰብ የሚፈልገውን መልዕክት በቀላሉ ለብዙሀን ለማስተላለፍ ካሻው ከፅሑፍ የተሻለ ነገር አማራጭ የለም፡፡ ሀሳባችንን፣ ስሜታችንን፣ ደስታችንን፣ ሀዘናችንን የሆነውን፣ ያሰኘነንን በመግለፅ ያለምንም ድካም የተፈለገውን ግብ መምታት ይቻላል፡፡ በተለይ በታዳጊ ሀገራት የታሻውን በቀላሉ ማግኘት ስለማይቻል መልዕክትን በቀላሉ ለሚመለከተው ክፍል ማድረስ ይከብዳል፡፡ በታክሲዎቻችንም ላይ የሚታየው ይኸው ነው፡፡ ባለታክሲዎቹ ተሳፋሪዎቹ ጋር የያዙትን ግብግብ፡፡ ከተሳፋሪ ጋር ያላቸው ቀረቤታ እና ቅራኖ ያሰለቻቸው ነው የሚመስለው በሚመስል መልኩ የተለጠፉት ጥቅሶችና አባባሎች በሙሉ ሹፌሩን እና እረዳቱን የሚደግፉ፣ የሚያበረታቱ አትንኩን የሚሉ ናቸው፡፡ እርግጥ ነው በራስ ንብረት ላይ ሌላን ማሞገስ እና ማወደስ ሊከብድ ቢችልም የአብዛኛው ታክሲ ነጂዎች ስሜት ይመሳሰላል፡፡
ጥቂት ታክሲዎች ላይ ቢሆንም ተሳፋሪን የሚደግፉ ፅሑፎች ተመልክቻለሁ፡፡

ልክ እንደጊዜውና ወቅቱ የአባባሎቹ እና ጥቅሶቹ ይዘትና ዓላማ ይቀያየራል፡፡ ብዙዎቹ ግን የሚያተኩሩት መንግስትን የሚቃወሙ፣ የሚደግፉ፣ የሀገር ፍቅርን የሚገልፁ፣ ሀይማኖታዊ ይዘት ያላቸው፣ ስፖርት ተኮር ናቸው፡፡
እነዚህ የታክሲ ላይ ፅሑፎች ድሮ በየጠጅ ቤቱና ጠላ ቤቱ ከሚፃፉት የሚለዩባቸው አንዳንድ ነጥቦች አሉ፡፡ በዋናነት ግን የድሮዎቹ በቀጥታም ቢሆን መልካም ስሜትን ለመፍጠር ይሞክራሉ፡፡ ማለትም ጠንክሮ ስለመስራት፣ መበደል ቢኖር መቻልን፣ ክፉ አለመመኘትን፣ እና የመሳሰሉትን ትንሽም ቢሆን ፈሪሃ እግዚአብሔርን ይሰብካሉ፡፡ አንባቢውም ይሁን  ጠጪው  በዚሁ ቀለበት ውስጥ ያለ ነው፡፡ እንዳሁኑ ባይሆንም ቦታ ይሰጡታል አሁን የምናያቸው ግን ከላይ ያልኳቸውን ነገሮች ያካተተ ቢሆንም ብዙዎቹ ግን ‹‹እኔነት›› ስሜት አለባቸው፡፡ አትንኩኝ፣ ሂዱልኝ የሚሉ ብሶታዊ አንድምታ አላቸው ፡፡ መማረርና ጨለምተኝነት ይሰብካሉ፡፡በእርግጥ መልካም ሀሳብንም የያዙ አሉ፡፡
አንዳንዶችም የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን ይጠቀማሉ፡፡ እነዚህም ቢሆኑ ከአቅም በላይ የሆነ ነገር እንዳለ ጠቋሚዎች ናቸው፡፡ ‹‹ለሚያልፍ ቀን ክፉ አትናገር›› . . . . ‹‹ የጌታ ፍቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን››. . . . ‹‹እግዚአብሔር ይፈርዳል›› . . .ወዘተ. . . መፅናናትን ተስፋ አለመቁረጥን አይዞን፣እንጠንክር ይላሉ፡፡ ፍርሃትን ፈጣሪዎች ናቸው፡፡በጊዜው ሁኔታ የፈጠረው እንደሆነ ባላውቅም ግን የሆነ የጎደለ ነገር እንዳለ ያሳያል፡፡

ስነፅሑፍ በጊዜያትና በትውልዶች መካከል በራሱ መንገድ የሚሄድና የሚለወጥ ጥበብ እንደመሆኑ የድሮን የአፃፃፍ ጥብበና ይዘት በዚህ ዘመን መጠበቅ የዋህነት ሊሆን ይችላል፡፡ ያም ቢሆን የምንፅፋቸው ነገሮች የራሳቸውን የሆነ መልዕክትና ተፅዕኖ ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ከግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል፡፡እኛም ሁሌም ልንማር፣ ልናውቅ ፣ ልንጠይቅ እራሳችንን የተሻለ ለማድረግ መጣር ይኖርብናል፡፡

ከማጠቃለሌ በፊተ ስለታክሲ ጥቅሶች ማውራታችን ካልቀረ እስቲ የታዘብካቸውንና ያነበብኳቸውንና ትንሽ ፈገግ ያደርጋሉ ያልኳቸውን ላካፍላችሁ፡፡

·    የታክሲ ከሌለህ ወርደህ በባስ ሂድ·  ሠውን ማመን ተፈራርሞ ነው·  ፍቅር ካለ ባጃጅ ባስ ይሆናል
·
   በቴሌቶን ሂሳብ መክፈል ክልክል ነው
·
   ሒሳብ ሳይከፍሉ ሀሳብ አይጀምሩ
·
   ለፀባይኛ ተሳፋሪ የፀባይ ዋንጫ እንሸላማለን
·   ለስራ ነው የወጣነው
·   በመጀመሪያ የጋለ ደምህን ተቆጣጠርና ሀሳብህን ግለፅ
·
    ባለጌና ዋንጫ ከወደአፉ ይሠፋል
·
   ኤች.አይ.ቪንና የጫማ ሽታን በጋራ እንከላከል
· 
 ማንችስተር ያሸንፋል አርሠናል ለዘለዓለም ይኑር
·   ሠው አካውንት ይከፍታል አንዳንዱ አፉን ይከፍታል
·   ሞባይል ለጣለ ሲም እንመልሳለን
·   ሹፌሩን መጥበስ ክልክል ነው በነገር
·  ሠው ብቻ ነው የምንጭነው በስህተት የገባ ይውረድ
·  ታክሲ ለሚጠቀሙ ብቻ 
·  ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ አስተያየት፣ቅሬታ፣ትዝብት ወይም መሻሻል አለበት የምትሉት ነገር ካለ     አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል::
·  ለሠው ቅን ሁን እንጂ ቅንቅን አትሁን
·  ማስቲካ የሚታደል መስሎአችሁ አፋችሁን እንዳትከፍቱ
·  መስኮቱን በመክፈት ለትራፊክ ፖሊስ አያጋፍጡን!
·  ጤነኛ ካልሆኑ መውረጃዎ ደርሷል
·  በጭነት መኪና መታችሁ እዚህ ትቀናጣላችሁ
·  የክፍለ ከተማ ሠዎች ካላችሁ ሒሳብ በቅድሚያ
·  ኑሮአችሁ ሳይሞላ "ታክሲው አልሞላም?! " ትላላችሁ!·  ጥብቅ ማሳሰቢያ ለክቡራን ሌቦች ሒሳብ ሰብስበን ሳንጨርስ ስራችሁን 
መጀመር አትችሉም! የማይስማማ ሌባ ካለ መውረድ ይችላል፡፡
·  ለዓለም ሙቀት መጨመር መንስዔው ጭቅጭቅ ነው
·  ይህ ታፔላ የሚሉት ከመጣ ፤ ምሳችን በቆሎ ራታችን ቂጣ
·  ታክሲው ሳይቆም መውረድ ይቻላል፡፡
·   እንዴት ጭት አትቃሙ ይባላል፣ ሰርቶ የማይዝናና አህያ ብቻ ነው

·  የበታችነት ከተሰማህ ዛፍ ላይ ውጣ
·  ስልጣን ህዝብን ማገልገያ እንጂ ማስፈራሪያ አይደለም
·  የቤትህን አመል እዛው!!!
·  የሠው ትርፍ የለውም . . . ተጠጋጉ!
·  በታክሲ. . . . .  ህግ አላውቅም
·  ታክሲና መንግስተ ሰማያት ሞልቶ አያውቅም
·  ለታላቅ መልስ አይሰጥም
·  ነገን ለመኖር መጀመሪያ ዛሬን ኑር..በመቃም
·  ‹‹ደሀ›› ከፍ ብሎ የሚታየው ባስ ላይ እና እራሱን ሲሰቅል ብቻ ነው፡፡
·  እባክዎን የአባይ ቃል ስላለብን ጠጋ ጠጋ ይበሉልን
·  ለካፌና ለላዳ ብዙ ይከፍላሉ፤ እኛ ጋ ሲሳፈሩ ለምን ይጨቃጨቃሉ

በመጨረሻ
ተሳፋሪ፡- የሰጠከኝ ልክ አይደለም፤ሒሳብ አትችልም
" ? አልተማርክምደደብ . . . .
ወያላ፡- ጋሼ  ድንጋይ ለመጫን እስከ ሁለተኛ ክፍል መማር በቂ ነው

አበቃሁ፡፡

21 comments:

  1. Nice view!!! I love reading the msg on the taxi, It's interesting!!! Keep it up!

    ReplyDelete
  2. Oh, It is cool, i like it very much

    ReplyDelete
  3. woooow, these people talk too much. It is somehow funny,but I am hoping they don't really use them in reality. Because some of them encourage thievs, not allowing expressing feeling, we will do whatever we want but you can't kinds of things....I still admire their creativity though. God bless you.

    ReplyDelete
  4. I really hate most of those words posted on the taxi, instead of saying 'thank you for using my taxi, they wrote a bunch of insulting words specially for women,"yebeteshin amel eziyaw", this is their favorite word/message. i hope one day they will change when there is competition with other transport sectors!
    thanks !

    ReplyDelete
  5. Enedene Emnet Yetaksilay Tiksoch Beabzagnaw Mekarina Astemari nachew. Yihm ende and edil yemikoter new. Beaznagn'netachew fegeg yemiyasengu tiksoch minalbat beliyou liyou mekniyatoch tekefto yemetan sew kebisichit metadegiya yihonalu biye asibalehu. Betechemarim be taksi lay yalut Ende "Yale dingil Mariyam Amalajinet Alem Aydinim, Siladereghelign hulu Ameseginalehu, Tsionen yemitelu yitsetsetalu, Hulum Bersu Hone,..." ena mesel tiksoch Wengel lealem endidares ena yetesasatut kesihtetachew endimelesu yerasun astewatsio yaberektal yemil Emnet alegn. Thanks alot!

    ReplyDelete
  6. Excellent web site you've got here.. It's difficult
    to find high-quality writing like yours these days. I honestly appreciate individuals like you!
    Take care!!
    Take a look at my web site read this blog

    ReplyDelete
  7. Nice blog here! Also your website loads up very
    fast! What host are you using? Can I get your affiliate
    link to your host? I wish my web site loaded up as quickly as yours lol
    my web site - click here link

    ReplyDelete
  8. Please let me know if you're looking for a author for your weblog. You have some really great posts and I believe I would be a good asset. If you ever want to take some of the load off, I'd
    love to write some articles for your blog in
    exchange for a link back to mine. Please blast me an email if interested.
    Kudos!
    My web site :: web hosting

    ReplyDelete
  9. so nice .........

    ReplyDelete
  10. The artiсle featureѕ νerified hеlpful to us.
    Ιt’s very informatіve and yοu're clearly quite well-informed in this region. You possess opened up my own face for you to varying opinion of this subject together with intriguing, notable and strong written content.

    Feel free to visit my blog: Xanax

    ReplyDelete
  11. wow betam teru nw bertalen

    ReplyDelete
  12. ብጣም የምራል ያልከው ልጅ ብጣም አስቀሀኛል :-)

    ReplyDelete
  13. Enter your comment...woooo i am realy like this

    ReplyDelete
  14. Enter your comment...wowww realy nice

    ReplyDelete