ሠላም ጤና ይስጥልኝ ክቡራን አንባቢያን ፤ ከዚህ መካነ-ድር (ድረ ገፅ) ላይ የምትወስዱትን ማንኛውንም ፅሑፍም ይሁን ምስሎች ለአዘጋጆቹ እና ለፀሐፊዎቹ ክብር ሲባል በምትጠቀሙበት ቦታ ሁሉ ምንጩን ትጠቅሱልን ዘንድ በትህትና እናሳስባለን ፡፡
Showing posts with label ካነበብኩት. Show all posts
Showing posts with label ካነበብኩት. Show all posts

Tuesday, September 17, 2013

“ከሠማይ የወረደው” መስቀል

ፀሐፊ፡አለማየሁ አንበሴ 
ምንጭ፡አዲስ አድማስ ጋዜጣ / መስከረም 4 ቀን 2006 . እትም

ከሌሊቱ 9 ሰዓት በቅድሰት ክርስቶስ ሠምራ ነዓለ ንግስ ላይ በምዕመናን መካከል ተገልፆ በቀስተ ደመና ብርሃን በመብረቅ ድምፅ የወረደው መስቀል
ምስል፡-አዲስ አድማስ ጋዜጣ

                               ወደ አቃቂ ከተማ ከሚያስገባው ዋና የአስፓልት መንገድ በስተግራ 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ገላን ጉራ በሚባለው ስፍራ የዛሬ 5 አመት የተቋቋመው የገብርኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ነሐሴ 23 ቀን የክርስቶስ ሰምራ በአለ ንግስ እየተከበረ እያለ ከሌሊቱ 9 ሰዓት የተከሰተው ግርግር ነው የዚህ ሁሉ መነሻ፡፡ ከባድ የፍንዳታ ድምጽ የሰሙ እና የቀስተ ደመና ቀለማትን የተላበሰ ብርሃን የተመለከቱ ነገሩን ከዝናባማው የአየሩ ሁኔታ ጋር በማያያዝ ብዙም ትኩረት አልሰጡትም ነበር የሚሉት የቤ/ክርስትያኑ መጋቢ፤ በነጎድጓድና በኢትዮጵያ ባንዲራ ቀለማት የታጀበ መስቀል ከሠማይ ሲወርድ አይቻለሁ ብለዋል፡፡ ከዚያን ጊዜ ወዲህ ባሉት ቀናት መስቀሉን ለማየት ወደ ቤተክርስትያኗ የሚጐርፉ ምዕመናን በርክተዋል፡፡
ባለፈው ሃሙስ ከአቃቂ ከተማ በማለዳ ተነስተን 2 ሠአታት የእግር ጉዞ በኋላ ከቤተ ክርስቲያኑ ስንደርስ፣ በጥቂት ምዕመናን ተሣታፊነት የእለቱ ቅዳሴ እየተከናወነ ነበረ፡፡ ከቆይታ በኋላ ግቢው ከየአቅጣጫው የመስቀሉን ታሪክ ሠምተው በመጡ ምዕመናን ተሞላ፤ መስቀሉ ከሰማይ ሲወርድ አይቻለሁ የሚሉት መጋቢ ሃዲስ ፍስሃ፣ ስለ መስቀሉ አወራረድ ገለፃ ማድረግ የጀመሩት ከቅዳሴው በኋላ ነው፡፡
ግቢው ውስጥ ከቤተ ክርስቲያኑ ህንፃ አጠገብ መስቀሉ የወደቀበትን ስፍራ እያመለከቱ ይናገራሉ -ቦታው በቆርቆሮ ታጥሮ ድንኳን ተተክሎበታል። መስቀሉ አርፎበታል ከተባለው ስፍራ አፈር እየቆነጠረ የሚቀርብላቸው ምዕመናን አፈር እየተመለከቱ የመጋቢ ሃዲስን ገለፃ ያዳምጣሉ፡፡ 

Sunday, September 9, 2012

የዘመን መለወጫ በዓል፤ ዕንቍጣጣሽ።


ፀሐፊ ፡አባታችን አለቃ አያሌው ታምሩ

መግቢያ።
        በኢትዮጵያ የእምነት ትምህርት እየሰፋና እየጸና የቆየ በመሆኑ ምክንያት ከትምህርትነት ዐልፎ ወደ ባህልነት ተለውጦአል። እንዲያውም አብዛኛው የእምነት ትምህርት ትምህርት ነው ከሚባል ይልቅ ባህል ነው በሚባለው ስሙ የታወቀ ሆኖ ይገኛል። የባህል ዘርፎች ከሆኑ የእምነት መገለጫዎች አንዱ በዓል ነው። በዓል በሞላው የሰው ዘር ዘንድ የባህል መሠረቶች ከሆኑት አንዱ ክፍል ነው። እምነት ያለው በእምነቱ፥ እምነት የሌለውም በልማዱ የባህል ሥነ ሥርዐት የሌለው የሰው ዘር የለም። ግን በመሠረቱ የባህል መነሻው እምነት ነው። እያደር እየዋለ ወደ ልዩ ልዩ ልማድ እየገባ መሠረቱን ለቆ ይገኝ እንደ ሆነ ነው እንጂ በዓል ሲባል መሠረቱ እምነት ነው። በእምነት ላይ ነው ሁሉም የሚመሠረተው። ከበዓላትም ተቀዳሚ ሆኖ የሚገኘውን የዘመን መለወጫ በዓልን ስንመለከት በልዩ ልዩ ክፍለ ዓለማት፥ በልዩ ልዩ የሰው ዘሮች ባህል ውስጥ የታወቀ፥ ጸንቶ የኖረና የሚኖር ሆኖ እናገኘዋለን። የሰው ልጆች እንደ ጠባያቸው፥ እንደ ባህላቸው፥ እንደ ልማዳቸው እና እንደ እምነታቸው መሠረት ያዳበሩት፤ አንዳንድ ጊዜም ነገሥታት ወይም አምባገነን መሪዎች በሚያመጡት የሥርዐት ጠቀስ ሁኔታ እየተፈጠረ ጸንቶ የኖረ የዘመን መለወጫ ሥርዐት በየአገሩ ይገኛል። በእምነት ክፍል ግን የምንመለከታቸው እጅግ አነስተኞች ናቸው። እነዚህ እምነቶች የሚቀራረቡበትም የሚለያዩበትም ነገር  አለ። ለምሳሌ ክርስቲያኖች ከአይሁድ ጋራ መሲሕ ይመጣል የሚሉትን በትንቢት እምነት ሲቀበሉ ከኖሩ በኋላ ጊዜው ሲደርስ፤ ጊዜ ደረሰ፥ ተስፋ ተፈጸመ፥ አምላክ ሥጋ ለበሰ ብለው በማመናቸው፤ እንዲሁም እግዚአብሔር በአካል ሦስት፥ በባሕርይ አንድ ነው፤ አብ ወልድን መንፈስ ቅዱስን አስገኘ፥ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ከአብ ተገኝተዋል፤ እንዲህ ቢሆን ግን መቅደም መቀዳደም፥ መብለጥ መበላለጥ የለም ብለው በማስተማራቸው ክርስቲያኖች የተለየ ፈለግ የሚከተሉ ናቸው። ይህም ስለ ሆነ እምነታቸው ጠባብ በር፥ ጠባብ መንገድ ይባላል። ጠባብ በር፥ ጠባብ መንገድ ይሁን እንጂ መጨረሻው ደግሞ መዝለቂያው ሕይወት መሆኑን ራሱ መድኃኒታችን ስለ ገለጠ የክርስትና እምነት ዘላቂ ሕይወት ያለውና የሚሰጥ መሆኑ የታመነበት ነው።

የዘመን መለወጫ በዓል።
                  የዘመን መለወጫ በዓልን በተመለከተ የተለያዩ የእምነት ክፍሎች የየራሳቸው መነሻ ምክንያት አላቸው።

Monday, March 19, 2012

ከአንዱ አቅጣጫ ሲሸነፍ ከሌላ አቅጣጫ ይነሣል


በዳንኤል ክብረት 
 ከዳንኤል እይታዎች ተወሰደ

     ወደ
 ዝቋላ አያሌ ወጣቶች ከአዲስ አበባ፣ ከደብረ ዘይት እና ከናዝሬት በመጉረፍ ላይናቸው፡፡ የእነዚህ ወጣቶች ወደ ቦታው መንቀሳቀስ ቢያንስ እሳቱን ወደ ገዳሙ ዘልቆበመነኮሳቱ መኖርያ እና በአብያተ ክርስቲያናቱ ላይ አደጋ ከማድረስ ታድገውታል፡፡ ወደወንበር ማርያም ከተጓዙት የውኃ ቦቴዎች በወጣቶች ኃይል በማጓጓዝ፣ እሳቱ በመጣበትአቅጣጫ የሚገኙ የተወሰኑ ዛፎችን በመቁረጥ እና ሣሩን በማንሣት እሳቱ እንዳይተላለፍ አድርገውታል፡፡ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት አካባቢ ተግ ካለ በኋላ በአሁኑ ሰዓት እሳቱ አጣብቂኝ እየተባለከሚጠራው ቦታ እስከ ዓርብ ረቡዕ ድረስ ባለው ቦታ ላይ ማምሻውን እንደገና የመጣሲሆን ወደ ገዳሙ እንዳዘልቅ ለማድረግ በአካባቢው የደረሱት ወጣቶች ነቅተው በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡በአካባቢው የሚገኙ የአደጋ ተከላካዮች እንደሚገልጹት እሳቱ አንድ ጊዜ እየቆመ ሌላ ጊዜካልታሰበበት አቅጣጫ ይመጣል፡፡ ይህም የመከላከሉን ሥራ ከባድ ያደረገው ሲሆን እሳቱጠፍቷል የሚል መረጃ እንዲሠራጭም አድርጓል፡፡

ክተት ወደ ዝቋላ


በዳንኤል ክብረት 

     ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን በመንደድ ላይ መሆኑን የገዳሙ አባቶች እየተናገሩ ነው፡፡ እሳቱ መንደድ ከጀመረ ወደ ሃያአራት ሰዓት ሊጠጋ ነው፡፡ መንግሥት ከአካባቢው የውኃ ቦቴዎችን እና ወታደሮችንበማንቀሳቀስ ውኃውን ለማጥፋት ጥረት እያደረገ ቢሆንም እሳቱ ግን ወደ ገዳሙ በመጠጋት ላይ ነው፡፡

አሁን
 አማራጫችን አንድ ብቻ ነው፡፡ የዝቋላን ገዳም ከማጣታችን በፊት ያለንን ነገር ሁሉ ይዘን በተገኘው ትራንስፖርት ወደ ዝቋላ መትመም ብቻ፡፡ ወንበር ማርያም ድረስ የውኃቦቴዎቹ ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለውን ባገኘነው ዕቃ ሁሉውኃውን ይዘን በመውጣት መረባረብ፡፡ ያለበለዚያ ግን የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ወደ ታሪክነት ይቀየራል፡፡

እነሆ
 ክርስትናችን የሚፈተንበት፣ ኢትዮጵያዊነታችንም የሚለካበት ጊዜ መጣ፣ በእሳትተቃጥለው ያቆዩትን ገዳም ከእሳት ማዳን ካልቻልን እንግዲህ የኛ መኖር ትርጉሙ ምንድን ነው?
መኪኖች ያሏችሁ አንቀሳቅሱ፣ ጉልበት ያላችሁ ተንቀሳቀሱ፣ ሌላም አማራጭ ያላችሁ በፍጥነት ተጓዙ፣እሳቱን በእምነት እንቅደመው፡፡

Sunday, February 5, 2012

ፆመ ነነዌ


በገብረእግዚአብሔር ኪደ
ማህበረ ቅዱሳን 
ነነዌ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪካቸው በስፋት ከተጻፈላቸው የሜሶፖታምያ ከተሞች አንዷ ናት፡፡ ብዙ የሥነ መለኲት ምሁራን ከዛሬዋ የሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ ሰሜን ምዕራብ 350 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ እንደ ነበረች ይስማማሉ፡፡ ምንም እንኳን በ4000 ቅ.ል.ክ. ገደማ በናምሩድ በኩል ብትቆረቆርም /ዘፍ.10፡11-12/ የአሦራውያን ዋና ከተማ የሆነችው ግን በ1400 ቅ.ል.ክ. ነው /2ነገ.19፡36/፡፡ በከተማዋ በጣም ታዋቂ የነበረው የጣዖት ቤተ መቅደስ የአስታሮት ቤተ መቅደስ ይባላል፡፡

 

በዚህች ከተማ የሚኖሩት ሰዎች የሚሠሩት ክፋትና ኃጢአት እጅግ ከመብዛቱ የተነሣ ጽዋው ሞልቶ መጥፊያቸው ስለ ደረሰ ለፍጥረቱ ርኅራኄ ያለው እግዚአብሔር ግን ንስሐ ይገቡ ዘንድ ነብዩ ዮናስን ልኮላቸዋል፡፡ ይህ ነብይ ከአሕዛብ ወደ አሕዛብ የተላከ ነብይ ነው፡፡ አላላኩም 

Monday, November 21, 2011

ይቺ ህዳር ወር. . . .


             ፀሐፊ፦አበበ ቶላ፤ የአቤ ቶኪቻው ሽሙጦች፣ 2002

  
    ይቺ ህዳር ወር እኮ ቀስ በቀስ በዓመት በዓሎች ተሞልታ ትርፍ ቀን ሊጠፋባት ነው፡፡ ‹‹ህዳር አጠና››፣ ‹‹ታላቁ ሩጫ››፣ ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች ቀን›› ኧረ ሌሎችም አይጠፉም፡፡

ባለፉት ሰሞናት ማጤሱን እርግፍ አድርጎ ትቶት የነበረው ወዳጄ ከኪሱ እንደዋዛ ሲጋራውን መዘዝ አድርጎ ለኮሰና ጭሱን አንቧለለብኝ፡፡

‹‹የተውከውን ሲጋራ ዛሬ ምን ተገኘና አነሳኸው?›› አልኩት ጢሱ ወደ ዐይኑ እንዳይገባ አንድ ዓይኑን ጨፍኖ በተለመደ ትህትና ፣ ‹ህዳር ሲታጠን› አለኝ፡፡ እና ጢሱን ወደ እኔ አንቧለለብኝ፡፡ (በልቤ ታዲያ የምታጥነው እኛን ነው እንዴ? እያልኩ በአፌ ዝም!)
በየዓመቱ ህዳር 12 ‹‹ህዳር ሲታጠን›› በርካታ የአገራችን ክፍል ይታጠናል፡፡ ለምን? ታሪኩ በከፊል የሚከተለውን ይመስላል፡፡

በዛ ዘመንም በአገሪቱ ሕመም በረታ በመላው አገሪቱ በሽታው እየተላለፈ በርካቶችን ለሞት ዳረገ፡፡ ሕፃን፣ ሽማግሌ ሳይለይ ለህመም እና ሞት የዳረገው ይህ ዘመን ለአገሪቱ ትልቅ ስጋት ሆነ፡፡ ምን ይደረግ? ሲሉ ሊቃውንት መከሩ፡፡ መከሩ እና ቆሻሻን ሰብስቦ በማቃጠል ህዳርን አጠኑት፡፡ ችግራቸውም ከጭሱ ጋር አብሮ በነነ፡፡ አንዳንዶች አሁንም ቢሆን ያሉብንን ችግሮች ለማቃለል ብቸኛው መፍትሔ ይኽ ሳይሆን አይቀርም ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ ለምሳሌ እንደ ኑሮ ውድነት፣ እንደ መልካም አስተዳደር እጦት፣ እንደ ሙስና የመሳሰሉት ህዳር ሲታጠን ይጠፋሉ የሚል እምነት በአንዳንድ ሰዎች ዘንድ አለ፡፡ ለምሳሌ ያ ወዳጄ የሲጋራውን ጢስ ወደ እኔ ያቦነነው ችግሬ አንተ ነህ ሊለኝ ፈልጎ ነው፡፡ ምን አደረኩት? ምንም፡፡ ከመምከር በስተቀር ምን የማድረግ አቅም አለኝ?

Monday, November 7, 2011

ምን ዓይነት “ኦርቶዶክስ” ነን?

በኤፍሬም እሸቴ
  
         “ፌስቡክ”ን መጠቀም ከጀመርኩበት ጊዜ ጀምሮ ብዙ ሰዎች “ሃይማኖት” የሚለው ቦታ ላይ የሚያስቀምጡትን ስመለከት እንዲሁም አንዳንድ የማላውቃቸው ሰዎች ወይም “የፌስቡክ ጓደኝነት” የሚጠይቁኝ ወዳጆቼ እነማን መሆናቸውን ለማወቅ የግል ማኅደራቸውን እና ማንነታቸውን ወደሚያሳየው ቦታ ስገባ እና ስለ ሃይማኖታቸው ሳነብ የሚገርም ነገር አይቻለኹ። ይህንን ጽሑፍ ለመጻፍ ያነሣሣኝ ደግሞ ተደጋጋሚነቱ ነው። እና እነዚህ ወዳጆቼ ሃይማኖት የሚለው ሥፍራ ላይ ሲጽፉ “ግሪክ ኦርቶዶክስ” ይላሉ። ሰዎቹ ግሪካውያን እንነዳልሆኑ ይታወቃል።
ምክንያቱም ግሪካዊነት በትውልድ የሚመጣ ዜግነት ነው። ማለት የፈለጉት ደግሞ ስለዜግነታቸው እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ነገሩ “ምን ዓይነት ኦርዶክስ እንደሆንን ያለመረዳት” ወይም “ኦርቶዶክስነታቸውን ለሌሎች ዜጎች የማስረዳት ችግር” መሆኑን ገመትኩኝ። ስለዚህም ነው “ምን ዓይነት ኦርቶዶክስ ነን?” ለማለት የፈለግኹት።