ከዘማሪ ‹ይልማ ሀይሉ› መዝሙር የተወሰደ
ህማሙን ልናገር አንደበት ቢያጥረኝም
መቼም ምንም ቋንቋ ለዚህ አይገኝም
ከረጅሙ ባጭር ከሰፊው በጠባብ
ስለከፈለልኝ ስለጌታ ላስብ
በጌቴ ሰማኔ ባታክልቱ ቦታ
ምድሪቷ ተሞልታ በታላቅ ፀጥታ
የአዳምን ልጅ ስቃይ በደሉን ሊሸከም
ጌታችን አዘነ ተጨነቀ በጣም
ሐዋርያት ደክመው ተኝተው ነበረ
ይሁዳ ከአይሁድ እንደተማከረ
ጭፍሮች እየመራ ጌታውን ሊያስገድል
የተሰራለትን ቸርነት ሳይቆጥር
ፋና እያበሩ ጭፍሮቹ ሲመጡ
ጌታን ሊያንገላቱት እንደዛ ሲቆጡ
የአምላኩን ጠላቶች መንገድ እየመራ
ይሁዳ ብቅ አለ ከቀያፋ ጋራ
